Dilla University

Dilla University
ዲላ ዩኒቨርሲቲ

Green University, Sustainable Future

News
ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

Top News

ዲ.ዩ፣ ጥር 10/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት እና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለይርጋጨፌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች የህፃናት ድንገተኛ ህክምናን፣ የጨቅላ ህፃናት እንክብካቤን እና የምግብ እጥረት ያለባቸው ህፃናት የህክምና አገልግሎትን ለማሻሻል የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል።
በስልጠናው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ተካልኝ አያሌው፣ በይርጋጨፌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ፤ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ አጠቃላይ ሆስፒታል የይርጋጨፌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን አቅም ለማጎልበትና ያለውን ችግር በመለየት፣ አብሮ ለመስራት በተቀመጠው አቅጣጫ ለህክምና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና በመደረጉ አመስግነዋል።
በዚህም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ስፔሻሊስት ሐኪሞችን በመላክ በሳምንት ሁለት ጊዜ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ በማድረግ የአከባቢው ማህበረሰብ በከፍተኛ ህክምና ፍላጎት ሳይጉላላ ተገቢውን ህክምና እንዲያገኝ እየተደረገ እንደሆነና ከዚህ በፊት ሲሰራ ያልነበረ የቀዶ ጥገና ሕክምና አገልግሎት መሰጠት መቻሉን ገልጸዋል። አያይዘውም፤ በህፃናት ድንገተኛ ህክምና ስፔሻሊስት ሐኪሞች ለህጻናት ተገቢው አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ፕሬዝዳንት ፤ በጤናው ዘርፍ ብዙ የሚሰሩ ስራዎች እንዳሉ አንስተው፤ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት እና አጋርነት ዳይሬክቶሬት የተቋሙ የትኩረት አቅጣጫ አንዱ በሆነው የጤና ዘርፍ ላይ ትኩረት አድርጎ ለሆስፒታሉ የህክምና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠቱን አድንቀው ሰልጣኞች በበኩላቸው ለጤና ጣቢያዎች እና ለጤና ኬላዎች ሙያዊ ድጋፍ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ስልጠናውን የሰጡት ዶ/ር እንየው መለሰ፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ አጠቃላይ ሆስፒታል የህፃናት እስፔሻሊስት ሐኪም እንዲሁም ዶ/ር ሀዊ መሐመድ የህፃናት ድንገተኛ ክፍል ሐኪም፤ በጨቅላ ሕፃናት እንክብካቤ እና የምግብ እጥረት ባለባቸው ሕጻናት ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙዎችን ለማብቃት የተሰጠ ስልጠና መሆኑን አብራርተዋል፡፡
የማጠናቀቂያ ላይ ንግግር ያደረጉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ሕክምና ሳይንስ ኮሌጅ አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ትዝአለኝ ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ሰልጣኞች ባገኙት እውቀትና ክህሎት ተጠቅመው ህሙማን በማገዝ ላይ አመርቂ የሆነ ለውጥ ማምጣት እንዲችሉ የተሰጠ ስልጠና መሆኑን ጠቅሰው፤ በቀጣይነት የተለያዩ አስፈላጊ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች እንደሚሰጡ ገልጸዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ አቶ ትዝአለኝ ፤የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለመጨመርም ሆነ ችግሮችን ለመፍታት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ገልጸው የአቅም ግንባታ ስልጠናው እንዲሳካ በማድረጉ የይርጋጨፌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማኔጅመንትን በማመስገን ሰልጣኞች ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት ህብረተሰብን ለማገልገል እንዲያውሉት አሳስበዋል።
ከሰልጣኞች መካከል የጨቅላ ህፃናት ክፍል ነርስ የሆኑት ሲስተር ብርአለም አብዲ እና ክሊኒካል ነርስ ረድኤት ብርሃኑ ከስልጠናው የተሻላ እውቀት እንደቀሰሙ ገልፀው፤ ይህን መሰል የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎች ለሌሎችም ባለሙያዎች ቢሰጡ ክፍተቶችን ለመሙላት እንደሚያግዙ ገልጸውልናል።
በአቅም ማጎልበቻ ስልጠናው ከሆስፒታሉ በድንገተኛ ክፍል፣ በጨቅላ ህፃናት ክፍል እና በምግብ እጥረት ክፍል የሚሰሩ 15 ባለሙያዎች መሳተፋቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

gtadmin