Dilla University

Dilla University
ዲላ ዩኒቨርሲቲ

Green University, Sustainable Future

News
ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

Top News

ዲ.ዩ፤ ሚያዝያ 17/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት ምርታማነታቸው በምርምር የተረጋገጠ የቡና ችግኞችን ከዱማርሶ ችግኝ ጣቢያ ለአርሶ አደሮች አሰራጭቷል።
ችሮታው አየለ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት፤ በእለቱ የመክፈቻ ንግግር አድርገው የቡና ችግኝ ስርጭቱን ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት ከዛሬ አምስት አመት በአካባቢው ተከስቶ የነበረው ውርጭ የአርሶ አደሩን ቡና አጥፍቶት ስለነበር በዛ መነሻነት ዲላ ዩኒቨርሲቲ ወደ ቡና ምርምር ስራ ገብቶ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ ተግባራትን እየፈጸመ እንደሆነ አስረድተዋል።
ዶ/ር ችሮታው፤ አክለውም ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ጊዚያት የቡና ችግኞችን እያለማ ለአርሶአደሩ ከማሰራጨት ባሻገር አርሶ አደሩንም ሆነ ወጣቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን በዘርፉ እንዲሰማሩ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
አቶ ታጠቅ ዶሪ፣ የጌዴ ዞን ም/አስተዳዳርና የግብርና መምራያ ኃላፊ በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት እንደ ዞን የቡና ችግኝ መትከል በትኩረት እየተሰራበት መሆኑን አንስተው፤ ዩኒቨርሲቲው ወቅቱን የጠበቀ በምርምር የታገዘ ምርትና ምርታማነቱ የተረጋገጠ የቡና ችግኝ አባዝቶ በነፃ ለአርሶ አደሮቻች ማደሉን አድንቀዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳሬክተር አቶ ተካልኝ ታደሰ፤ በዘንድሮው የምርት ዘመን በአጠቃላይ በ5 ጣቢያዎች 442 ሺህ የቡና ችግኞች ለ816 አርሶ አደሮች ለማሰራጨት መታቀዱን ተናግረዋል። ከዚህም መካከል በዚህ የስርጭት መርሃ ግብር በይርጋጨፌ ዱማርሶ የችግኝ ጣቢያ 190 ሺህ ችግኞች ለ305 አርሶ አደሮች መሰራጨቱን ገልፀው በቀጣይ ቀናት ሌሎች ጣቢያዎች ላይ ያሉትም እንደሚሰራጩ ተናግረዋል።
በመርሃግብሩ ላይ የመዝጊያ ንግግር ያደረጉት ዱላ ቶሌራ (ዶ/ር) የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር የምር/ማህ/ጉድኝት ዋና ስራ አሰፈፃሚ ተወካይ፤ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያሉበትን አከባቢ ማህበረሰብ በምርምር ማገዝ አንዱ ተግባራቸው መሆኑን ገልፀው፤ የዲላ ዩኒቨርሲቲ እየሰራ ያለው ስራ በሞዴልነት የሚያስጠቅስ ነው ሲሉ ገልጸዋል።
በወቅቱ የቡና ችግኝ ሲወስዱ ያገኘናቸው አቶ ደሳለኝ ገመዴና አቶ ዳዊት ግዛው በበኩላቸው፤ ከዚህ በፊት ከወሰዱት የቡና ችግኝ ጥሩ ምርት እንዳገኙ ጠቅሰው ዘንድሮም ለዚህ እድል ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል።
በእለቱም ቡናቸው በማርጀቱና ምርታማነቱ በመቀነሱ ያረጁ የቡና ተክሎችን በመንቀል ከዩኒቨርስቲው ያገኙትን የቡና ችግኝ ለመትከል ማሳቸውን ባዘጋጁ አርሶ አደሮች ማሳ ላይ የቡና ችግኝ ተከላ ተከናውኗል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et

gtadmin