Dilla University staff members attend a project meeting with UiT, the Arctic University of Norway

DU: September 19, 2023 (P.I.R.): As part of the staff-exchange program of the NORPART Project, won by Dilla University and UiT, five staff members of Dilla University have been in Tromso for a week. They have also held successful project meetings, seminars, and guest lectures with the UiT staff.

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት የ2016 የትምህርት ዘመን ስራን አስጀመረ

ዲ.ዩ፦  መስከረም 07/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኮሚኒት ትምህርት ቤት የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል። 

ብቃትና ጥራት ያለው ዜጋ ለማፍራት ትምህርት ለአንድ ሀገር ወሳኝ መሆኑን የገለፁት፤  የኮሚኒቲ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የወላጅና መምህራን ህብረት ሰብሳቢ ዮናታን አየለ(ዶ/ር)፤ ትምህርት ቤቱ ዝግጅቱን አጠናቆ  ወደ ስራ መግባቱን ገልጸው፤ አዲሱን የትምህርት ፖሊሲ ሙሉ በሙሉ ለመተግበር ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አንስተዋል።

ዶ/ር ዮናታን አክለውም፣ ባለፈው አመት እንደ ሀገር ያለው ውጤት አጥጋቢ ባይሆንም የኛ ትምህርት ቤት አፈፃፀም የተሻለ ነበር ሲሉ አንስተዋል። አሁን ከዞን ባለፈ በክልል ደረጃ ከሌሎች ትምህርት ቤቶች ጋር ለመወዳደር እየሰራን እንገኛለን ሲሉ ዶ/ር ዮናታን ተናግረዋል።

የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቅርስ ኮሚቴ የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ወስኗል

ዲ.ዩ፦ መስከረም 06/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፤ የተባበሩት መንግስታት የዓለም ቅርስ ኮሚቴ በጌዴኦ ዞን የሚገኘው የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድርን በመንግስታቱ የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ ውስኗል።
ኮሚቴው ዛሬ ባካሄደው 45ኛ ጉባኤው የጌዴኦ ባህላዊ መልክዓ ምድር ያለውን ከፍተኛ ዓለም አቀፍ ፋይዳ ታሳቢ በማድረግ በዩኔስኮ በዓለም ቅርስነት እንዲመዘገብ መወሰኑን ነው ያስታወቀው።
በጉባኤው ከኢትዮጵያ የተገኙት የቱሪዝም ሚኒስትር አምባሳደር ናሲሴ ጫሊ እና የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር) ስለ ጌዴኦ ማኅበረሰብ አኗኗር እና ባህላዊ መልክዓ ምድሩ ለተሳታፊዎች ማብራሪያ መስጠታቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።

ለድህረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ!

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከዚህ ቀጥሎ በተያያዘው ማስታወቂያ በተዘረዘሩት የትምህርት አይነቶች በ2016 ዓ.ም በመደበኛው መርሃግብር ለሁለተኛ (MA/MSc) እና ለሶስተኛ (PhD) ዲግሪ ትምህርት አመልካቾችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።
የማመልከቻ ጊዜ፦ ከነሐሴ 10/2015 ዓ.ም እስከ መስከረም 05/2016 ዓ.ም። የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ወደ ፊት የሚገለፅ ይሆናል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ሆሲፒታል በክረምት የበጎ ፈቃድ ነጻ ህክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው

ዲ.ዩ፤ ነሐሴ 03/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ሆሲፒታል በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከፍለው መታከም ለማይችሉ የማህበርሰብ ክፍሎች ለተከታታይ ሁለት ሳምንት የሚቆይ ነጻ የጤና ምርመራ፣ የህክምና እና ምክር አገልግሎት እየሰጠ ነው። በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ከአራት ሺህ ሁለት መቶ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተደራሽ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።
ዶ/ር ዘመኑ አሸብር፣ የሆስፒታሉ ጥራት ቁጥጥር ኦፊሰር እና የክረምት በጎ ፍቃድ ነጻ ህክምና አገልግሎት አስተባባሪ እንደገለጹት፤ የበጎ ፈቃድ ነጻ የህክምና አገልግሎቱ እስከ ነሐሴ 14/2015 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ መሆኑን ተናግረዋል።

ለታካሚዎች የሚሰጠውን የህክምና አገልግሎት ጥራት ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፤ ነሐሴ 01/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል በተለይም ነርሶች ለህሙማን የሚሰጡትን አገልግሎት ጥራት ለማሻሻል እና ደረጃውን የጠበቀ ለማድረግ (Nursing Care Standard) የሚረዳ ሥልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
ስልጠናውን በዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል ከጤና ሚኒስቴር ጤና ማሻሻያ ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ማዘጋጀቱ ተገልጿል።

በሁለት ዙር ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተጠናቋል፤ ተማሪዎችም ወደየአካባቢያቸው ተሸኝተዋል

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 28/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፤ በአገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ በሁለት ዙሮች ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በሁለት ዙር ሲሰጥ የቆየው ብሄራዊ ፈተና መጠናቀቁን አስመልክቶ፤ ችሮታው አየለ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እንዲሁም ወ/ሮ ፈንቱ ኤልዶ፣ በትምህርት ሚኒስቴር የስርዓተ ትምህርት ዝግጅት ከፍተኛ ባለሙያ እና በፈተናው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጉድኝት ማዕከል ኃላፊ በጋራ መገለጫ ሰጥተዋል፡፡

Pages