Dilla University

Dilla University
ዲላ ዩኒቨርሲቲ

Green University, Sustainable Future

News
ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

Top News

ዲ.ዩ፣ መጋቢት 27/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክቶሬት የተሻሻሉና ምርታማነታቸው በምርምር የተፈተሸ የእንሰት ዝርያዎችን ስርጭት አካሂዷል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ም/ኘሬዝዳንትና የዩኒቨርሲቲው ኘሬዝዳንት ተወካይ ደረጄ አንዱዓለም (ዶ/ር)፤ አርሶ አደሩ በማሳው የሚተክላቸው የእንሰት ዝርያዎች በውስን ቦታ በቂ ምርት የሚሰጡ መሆኑን ገልፀው፤ ለአርሶ አደሩ የተሰራጩት የእንሰት ዝርያዎች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ገቢውን ለማሳደግ ብሎም ቴክኖሎጂን ለማስተላለፍ እንደሆነ ገልጸዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ኘሬዝዳንት ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ እንሰት ለቡና ምርታማነትም ሆነ ለመሬት ለምነት ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለውና ድርቅን በመቋቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያለው ተክል መሆኑን አንስተው ለአርሶ አደሮች መሰራጨቱን ገልጸዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተካልኝ ታደሰ በበኩላቸው፤ ለዚህ ውጤት የበቃነው በዩኒቨርሲቲው ምሁራን እና በወረዳው ቀና ትብብር መሆኑን አንስተው፤ ይህንን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የይርጋጨፌ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ክፍሌ ጅግሶ፤ ወረዳው በቡና እና በእንስት ምርት የሚታወቅ መሆኑን አንስተው፤ ዩኒቨርሲቲው በምርምር የተሻሻለ ምርት የሚያሰጥና የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ብሎም ገቢውን ከፍ ለማድረግ እየሰራ ያለውን ስራ አድንቀዋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሆልቲካልቸር ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ መምህር ጨምር ጨዋቃ፣ በዱማርሶ የችግኝ ጣቢያ የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች በወረዳው ለአራት ቀበሌያት ለእያንዳዱ ቀበሌ 16 አርሶ አደሮች በድምሩ 64 አርሶ አደሮች እያንዳዳቸው 35 የእንሰት ችግኞች እንዲሁም ለትምህርት ቤቶች 225 የእንሰት ችግኞች መሰራጨታቸውን ተናግረዋል።
የተሻሻለ የእንሰት ዝርያ ከተረከቡት መካከል አቶ ስለሽ ጠቀቦ ከቆንጋ፣ እንዲሁም ወ/ሮ አበራሽ ነጋሽ ከዶማርሶ፣ በምርምር የለሙ የእንሰት ችግኞችን ማግኘታቸው እንዳስደሰታቸው ተናግረው ዩኒቨርሲቲው የአርሶ አደሩን ህይወት ለመለወጥ እያደረገ ያለውን እገዛ ማድነቃቸውን ገልጸውልናል።
በቀጣይም በሌሎች የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማዕከላት የተሻሻሉ እና ውጤታማነታቸው በምርምር የተረጋገጡ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች እንደሚሰራጩ ለማወቅ ተችሏል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et

gtadmin

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *