Dilla University

Dilla University
ዲላ ዩኒቨርሲቲ

Green University, Sustainable Future

News
ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

Top News

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 27/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የመምህራን እና ተመራማሪዎችን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ በምርምር ጽሁፍ ረቂቅ አጻጻፍ፣ በአሳታሚ ምርጫ እና በማሳተም ዙሪያ በሃሴ ዴላ ግቢ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ምስጋኑ ለገሰ (ዶ/ር)፣ የምርምር፣ ህትመት፣ ስነ ምግባርና ሥርፀት ዳይሬክተር፤ በዩኒቨርሲቲው በርካታ ምርምሮች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸው፤ ተመራማሪዎች ስራዎቻቸውን እንዴት እውቅና ባላቸው ጆርናሎች በማሳተም ወደ አለም አቀፍ የሳይንስ ማህበረሰብ ማቅረብ ይችላሉ ከዚያም አልፎ የተቋሙን ስም እንዴት ያሳድጋሉ የሚለውን የሚያሳይ ስልጠና እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
አቶ ታሪኩ ሎራቶ፣ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን እና የኢኮኖሚክስ ት/ክፍል መምህር በበኩላቸው፤ ኮሌጁ በዩኒቨርሲቲው ካሉ አንጋፋ ኮሌጆች መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፤ በኮሌጁ መምህራን በምርምር ዘርፍ በዩኒቨርሲቲ የሚደገፉ ከ50 በላይ ምርምሮች እየተሰሩ እንደሚገኙና እነዚህ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ጥናቶች አለም አቀፍ ጆርናሎች ላይ መታተም ስላለባቸው የመምህራንን የምርምር ስራዎችን የማሳተም አቅም ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ ስልጠና እንደሆነ ተናግረዋል።
ስልጠናውን የወሰዱ በህዝብ አስተዳደር ልማት አመራር ት/ክፍል መምህርት ማህሌት ገ/መስቀል፤ አርቲክሎችን እንዴት ማዘጋጀት እና ማሳተም እንደሚቻል እውቀትና ክህሎት ያገኘሁበት ስልጠና ነበር ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተውናል፡፡
በኢኮኖሚክስ ት/ክፍል መምህር የሆኑት አቶ ጋረደው አወቀ በበኩላቸው፤ ከመማር ማስተማር ጎን ለጎን በምርምር በመሳተፍ የምርምር ስራዎችን የማሳተም ሂደቶች ምንድን ናቸው፣ የምርምር አርቲክል እንዴት ይጻፋል፣ ጥሩ አሳታሚ ጆርናሎችን እንዴት መምረጥ ይቻላል በሚሉ ጉዳዮች ዙሪያ ጥሩ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀውልናል፡፡
ከ50 በላይ የሚሆኑ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ መምህራን እና ተመራማሪዎች ስልጠናውን መከታተላቸው ታውቋል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et

gtadmin