Dilla University

News
Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call For Papers

Call For Papers

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 26/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ለተማራማሪዎች፣ ለውስጥ ሰራተኞች እና ለባለድርሻ አካላት በቡና ጥራት ቅምሻ ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል።
ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት በስልጠናው መክፈቻ ባደረጉት ንግግር፤ በቡና ስራ የተሰማሩ አርሶ አደሮች፣ ነጋዴዎች እና ባለድርሻ አካላት ከዘርፉ ተገቢውን ትርፍ እንዲያገኙ፣ የስራ እድልና ሀብት ፈጠራን በማስፋት ለሀገር እድገት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ ዲላ ዩኒቨርሲቲም ቡናን በመማር ማስተማር፣ በምርምር እና በማሕበረሰብ አገልግሎት ስራዎች በማካተት እየሰራ እንደሚገኝ አንስተዋል።
ለተመራማሪዎች፣ ለመምህራን እና ለሰራተኞች የተዘጋጀውን ስልጠና በቀጣይ አጠናክሮ በመቀጠል ያለውን አቅም በማስፋት ዘርፉን የቤተ ሙከራ፣ የተግባር ስራና የምርምር ስራዎች በመስራት የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ተግባራዊ የሚሆንበት የልህቀት ማዕከል ለማድረግ ጥረት እንደሚደረግ ዶ/ር ሀብታሙ አያይዘው ገልጸዋል።
አለሙ ደሳ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክተር በበኩላቸው፤ ዩኒቨርሲቲው በሀገርና በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ቡና የሚመረትበት አካባቢ የሚገኝ በመሆኑ ለቡና ልማት ትኩረት በመስጠት የተለያዩ ስራዎች በመከወን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው ቡና ለሀገራችን የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ለብዙ ሚሊዮን ህዝብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የገቢ ምንጭ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ ስልጠና በተቋሙ ስር የሚገኙ ተመራማሪዎች፣ ሰራተኞች እና ባለድርሻ አካላት በቡና ጥራት ቅምሻ የተሰጠ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑን ዶ/ር አለሙ አያይዘው ገልጸዋል።
መምህር ኩምሳ ወልደጊዮርጊስ፣ በቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም የስልጠና አስተባባሪ፤ የስልጠናው ዓላማ በተቋሙ ስር ያሉ ተመራማሪዎች፣ መምህራንና ሰራተኞች በንድፈ ሀሳብ ደረጃ የሚያውቁትን በተቋሙ ውስጥ በተደራጀው የቡና ጥራት መፈተሻ ቤተሙከራ ውስጥ የቡና ጥራት በቅምሻ በመለየት ተግባራዊ የሆነ እውቀት ለማዳበር መሆኑን አስረድተዋል።
እንደ መምህር ኩምሳ ገለጻ፤ ስልጠናው ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዲላ ቅርንጫፍ በዘርፉ በቂ እውቀትና ልምድ ያላቸውን ባለሙያ በመጋበዝ ከንድፈ ሀሳብ ጀምሮ በተግባር የቡና ጥራት በመለየት ዙሪያ ለተከታታይ ሶስት ቀናት ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል።
አቶ ተካልኝ መንገሻ፣ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ በዲላ ቅርንጫፍ ጥራት ተቆጣጣሪ፤ በስልጠናው የቡና ጥራት የሚያጓድሉ ሁኔታዎች፣ የቡና ጥራትን እንዴት መጠበቅ እንደሚቻል፣ ከችግኝ ተከላ ጀምሮ እስከ ቡና ቁሌትና ማፍላት ድረስ ያለውን ሂደት በንድፈ ሀሳብ ተጀምሮ በቤተ ሙከራ በተግባር የተደገፈ በቂ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስልጠና መሰጠቱን ገልጸዋል።
አቶ ተካልኝ አክለው፣ የቡና ምርታማነትን ለማሳደግና የቡና ጥራትን በማስጠበቅ ለአካባቢውና ለሀገር የሚያበረክተውን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ከፍ ለማድረግ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ የጀመረውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
ስልጠናውን ከወሰዱ መምህራን መካከል መምህር ጨምር ጨዋቃ፤ ስልጠናው ተግባር ተኮር የሆነ ከሙያቸውና ከሚሰሩት ምርምር ጋር የሚሄድ ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት የሚሰጥ እንደነበር አስተያየታቸውን ሰጥተውናል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *