Dilla University

News
Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call For Papers

Call For Papers

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ ጥር 10/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ አገልግሎት እና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለጌዴኦ ዞን፣ አባያና ዳራ ወረዳዎች የስፖርት ባለሙያዎች በእግር ኳስ አሰልጣኝነት እና ዳኝነት ሙያ ዙሪያ ለተከታታይ 5 ቀናት የቆየ ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል፡፡
በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ብሩህ ተስፋሁን፣ የዲላ ዩኒቨርስቲ የማህበረሰብ አገልግሎት እና አጋርነት ዳይሬክቶሬት የስልጠናዎች አስተባባሪ እንደተናገሩት፤ ስልጠናው ቀስፖርቱ ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎች በእግር ኳስ እውቀትና ክህሎት እንዲያዳብሩ፣ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የስፖርት ህጎችን አውቀው የአሰልጣኝነትና የዳኝነት ልምዳቸውን እንዲያሳድጉ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
ሰልጣኞች በአካባቢያቸው በየትምህርት ቤቶች ፕሮጀክቶችን በማቋቋም የወሰዱትን ስልጠና ወደ ተግባር እንዲቀይሩ ጭምር ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን አቶ ብሩህ አስገንዝበዋል።
ከአሰልጣኞች መካከል በዩኒቨርስቲው የስፖርት ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት መምህር ቸርነት ዳዊት እና መምህር አባያ ተፈራ እንደገለፁት፣ በእግርኳስ ስፖርት አሰልጣኝነትም ሆነ ዳኝነት በየጊዜው የሚደረጉ የህግ ለውጦችን ሰልጣኞች በአግባቡ እንዲያውቁና በየአካባቢው የሚደረጉ ጨዋታዎችን እንዲመሩ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በስልጠናው መዝጊያ ንግግር ያደረጉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክተር አቶ ተካልኝ ታደሰ በበኩላቸው፤ ስልጠናው የክህሎትና የእውቀት ክፍተት ለመሙላት የተሰጠ ስልጠና በመሆኑ ስልጠናውን የወሰዱ ሰልጣኞች ከስልጠናው ያገኙትን ክህሎት ወደ መሬት እንዲያወርዱና ተጨባጭ ስራ እንዲሰሩ አሳስበዋል።
ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል የዲላ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ስፖርት መምህርት ምስጋና አንዳርጌ እና በይርጋጨፌ ወረዳ የዶማርሶ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የስፖርት መምህር ሀብታሙ አለሙ እንደተናገሩት፤ ስልጠናው አዳዲስ የእግር ኳስ ህጎችና ቴክኒኮችን ያወቁበት፤ እንዲሁም በንድፈ ሃሳብ ያውቁት የነበረውን በተግባር ያዩበት እንደነበር ነግረውናል።
በስልጠናው ከጌዴኦ ዞን ስምንት ወረዳዎችና አምስት ከተማ አስተዳደሮች፣ ከሲዳማ ክልል ዳራ ወረዳ እና ከምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ የተውጣጡ አጠቃላይ 30 ሰልጣኞች ተሳታፊ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ዲላ ዩኒቨርሲቲ
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት