Dilla University

News
Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call For Papers

Call For Papers

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ የካቲት 06/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም አጋማሽ ላይ ከየካቲት 6 -11 የሚሰጠውን አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በዛሬው እለት መስጠት ጀምሯል።
ታምራት በየነ (ዶ/ር )፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንትና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ፤ በዩኒቨርሲቲው ዘንድሮ በ2016 ዓ.ም አጋማሽ ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና እንደ ተቋም በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ ሰፊ ቅድመ ዝግጅቶች መደረጋቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ታምራት አያይዘውም፤ በመውጫ ፈተናው ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት 393 የዲላ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተመራቂዎች፣ 457 ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመጡ እጩ ተመራቂዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትነው ዘንድሮ ዳግም የሚፈተኑ 206 ተማሪዎች፤ በአጠቃላይ 1057 እጩ ምሩቃን እስከ የካቲት 11 ድረስ የመውጫ ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል።
ለዚህም በዩኒቨርሲቲው አብይ ግብረ ኃይል እና ንዑሳን ግብረ ኃይሎች ተቋቁምው ወደ ስራ በመግባት ፈተናውን በአግባቡ ለመስጠት የሚያስችሉ ተግባራትን በማከናውን በፎረሞች ጭምር በማስገምገም ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ዶ/ር ታምራት ተናግረዋል።
እንደ ዶ/ር ታምራት ገለፃ፤ በዩኒቨርሲቲው በመደበኝነት ለሚፈተኑ ተማሪዎች ትምህርት ሚኒስቴር ከሰጠው የሞዴል ፈተና ባሻገር ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ለማስቻል የተለያየ የማካካሻ ትምህርት (Tutorial) እንዲሁም እስከ 3 የሚደርሱ የሞዴል ፈተናዎች እንዲወስዱ መደረጉ ታውቋል።
በዩኒቨርሲቲው የአይ ሲቲ ዳይሬክተር መ/ር በቀለ ወርቁ በበኩላቸው፤ የመውጫ ፈተናው በተሳካ ሁኔታ እንዲሰጥ አጠቃላይ የኮምፒተር፣ የኔትወርክና ሌሎች አስፈላጊ መሰረተ ልማቶች በበቂ ሁኔታ መሟላታቸውን ጠቁመው፤ ለዚህም በዋናው ግቢ ላይ መጠባበቂያ ክፍሎችን ጨምሮ በእያንዳንዳቸው 22 ኮምፒተሮችን የሚይዙ 14 የመፈተኛ ክፍሎች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
መ/ር በቀለ አክለውም፤ ይህ የመውጫ ፈተና የሚሰጠው አሁን ላይ በዋናው (ኦዳያአ) ግቢ ላይ ብቻ ቢሆንም ምናልባት ከተማሪ ቁጥር ጋር ተያይዞ አንዳንድ መጨናነቆች ቢፈጠሩ ለመጠባበቂያ በቀድሞ ዋና ግቢ ላይ ተማሪዎችን መፈተን የሚያስችሉ 5 የመፈተኛ ቦታዎች ዝግጁ መደረጋቸውን ተናግረዋል።
ፈተናውን ለሚወስዱ አጠቃላይ ተማሪዎች ዲላ ዩኒቨርሲቲ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።