Dilla University

News
Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call For Papers

Call For Papers

Green University, Sustainable Future

Uncategorized

ዲ.ዩ፤ የካቲት 19/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማሕበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብዕ ኮሌጅ ለስምንት የሥነ-ዜጋና ሥነ ምግባር የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ላፕቶፕ ኮምፒዩተር በስጦታ አበርክቷል።
ኢዮብ ቀለመወርቅ (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማሕበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብዕ ኮሌጅ ዲን፤ እንደገለጹት የሥነ -ዜጋና ሥነ ምግባር ትምህርት ክፍል ተማሪዎች የነበረባቸውን የኮምፒዩተር ችግር በመረዳት የትምህርት ክፍሉ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር የኔነሽ ተመስገን በስራ ጉዳይ ወደ አሜሪካ በሄዱበት ጊዜ በጎ አድራጊ ኢትዮያዊያን በማስተባበር ስምንት ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ገዝተው ለተማሪዎች አበርክተዋል።
ዶ/ር ኢዮብ አክለውም፤ ሀሳቡን አመንጭተው አቅደው ወደ ተግባር ለቀየሩት ዶ/ር የኔነሽና ሀሳባቸውን ተቀብለው ለበጎ አላማ እጃቸውን ለዘረጉት ለወ/ሮ ገነት አስራት እና አቶ ታምራት አወይቱ ምስጋና አቅርበዋል።
የኔነሽ ተመስገን (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሥነ ዜጋና ሥነ ምግባር ትምህርት ክፍል መምህርት፤ ተማሪዎች ፕሮጀክቶችን እና ምርምሮችን ለመስራት የኮምፒዩተር ችግር እንዳለባቸው በመረዳት በስራ አጋጣሚ ወደ ሀገረ አሜሪካ በሄዱበት ወቅት ያገኟቸውን በጎ አድራጊ የሆኑትን ወ/ሮ ገነት አስራት እና አቶ ታምራት አወይቱን በማነጋገር ስምንት ላፕቶፕ ኮምፒውተሮችን በማምጣት ለተማሪዎች በስጦታ እንዳበረከቱላቸው ገልጸዋል።
አቶ መሳይ ፍቅሩ፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ፤ በስጦታ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፣ የምናስተምራቸው ተማሪዎች የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ እና ማሕበራዊ ጫናዎችን ተቋቁመው የነገ ህልማቸውን እውን ለማድረግ ጥረት እያደረጉ መሆኑን መረዳት እንደሚያስፈልግ አስታውሰው፤ አስተዋይና ሙያውን የሚያከብር አስተማሪ ለተማሪዎቹ የቀለም ትምህርት መስጠት ብቻ ሳይሆን ተማሪዎቹ ያለባቸውን የግልና የጋራ ችግር ቀርቦ በመረዳት ችግሮችን ለመፍታት የበኩሉን አስተዋፅኦ የማድረግ ኃላፊነት እንዳለበት ገልጸዋል።
አቶ መሳይ አክለውም፤ ሀሳቡን በማንሳት ወደ ተግባር እንዲቀየር ላበቁት ዶክተር የኔነሽ ተመስገን እንዲሁም ሀብታቸውን ለወገናቸው ቀና ተግባር እንዲውል በማሰብ ኮምፒዩተሩን ገዝተው ለላኩት ወ/ሮ ገነት አስራት እና አቶ ታምራት አወይቱ እንዲሁም ኮምፒተሩ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገባና ለተማሪዎች እንዲደርስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ዶክተር ኢዮብ ቀለመወርቅና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ዲላ ዩኒቨርሲቲ ምስጋናና እውቅና እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ስጦታው ከተበረከተላቸው ተማሪዎች መካከል አስናቀ ጋቢሶ እና ታደለ ቱማቶ በሰጡን አስተያየት፤ የተበረከተላቸው ላፕቶፕ ኮምፒውተር የነበራቸውን የኮምፒዩተር ችግር በመቅረፍ የቀረውን የትምህርት ጊዜቸውን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚያግዛቸውና የምርምር ስራቸውን በቀላሉ ለመከወን እንደሚያስችላቸው ገልጸው፤ ሀሳቡን ላመነጩ መምህርታቸው እንዲሁም ድጋፉን ላደረጉ ግለሰቦች፣ ለትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ ለኮሌጁ ኃላፊዎች እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
FB: https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram:https://t.me/dprd9
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *