Dilla University

News
Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call For Papers

Call For Papers

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 09/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክቶሬት ከጌዴኦ ዞን፣ ከምዕራብ ጉጂ አባያ ወረዳ እና ከሲዳማ ክልል ዳራ ወረዳ ለተወጣጡ የባህልና ቱሪዝም ባለሙያዎች በሀገር በቀል ዕውቀት ዙሪያ ሰልጠና ሰጥቷል፡፡
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የጌዴኦ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ደርቤ ጅኖ፤ ኢትዮጵያ ሀገራችን በርካታ ሀገር በቀል እውቀቶች ባለቤት በመሆኗ እነዚህን አገር በቀል እውቀቶች ጠብቀን ማቆየት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ ደርቤ አክለውም፤ የማህበረሰቡ የተለያዩ እሴቶችና ልዩ ልዩ ቅርሶች ተጠብቀው ለትውልድ በማስተላለፍ ትውልድ እንዲማርበት ታስቦ የተዘጋጀው ስልጠና መሆኑን አንስተዋል። ከስልጠናው በኋላ ለቅርሶች ያለንን ግንዛቤን በመጨመር ለትውልድ እውቀታችሁን ማሸጋገር ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
አቶ ተካልኝ ታደሰ፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክተር በበኩላቸው፤ ባህልና ቅርስን አስጠብቆ ማቆየት መልካም አጋጣሚ በመሆኑ አሁን ላይ ያሉ ቅርሶችን የማስጠበቅ ስራ ከሚፈጥረው ከኢኮኖሚዊ ተጠቃሚነት አንጻርም መታየት እንደሚገባው አሳስበዋል።
ማህበረሰቡ በአካባቢው የሚገኙ ባህልና ቅርሶችን መጠበቅና መንከባከብ ብሎም ለትውልድ እንዲተላለፍ መስራት ይገባል ሲሉ አቶ ተካልኝ አያይዘው ተናግረዋል።
ስልጠናውን ከሰጡት መካከል ዶ/ር አብዮት መብራቴ፣ የዲላ ዩኒቨርሲት የሀገረሰብ ጥናት ተቋም ዳይሬክተር፤ ለራሳችን ቅርሶችና ባህል ያለን አመለካከት እንዲያድግ በማድረግ የሚኖረውን የውጭ ባህል በባህላችን እና በቅርሶቻችን ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይፈጥር መስራት እንደሚገባ መክረዋል።
ስልጠናውን ሲከታተሉ ያገኘናቸው ሰልጣኞች በቂ እውቀትና ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልጸው ዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢው ሀገር በቀል ዕውቀቶች ለቀጣይ ትውልድ እንዲተላለፉ እየሰራ ያለውን ስራ አድንቀዋል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et