Dilla University

Dilla University
ዲላ ዩኒቨርሲቲ

Green University, Sustainable Future

News
ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት በይፋ ተጀመረ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

ለአርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

Dilla University and ReWork Inc. Sign MOU to work in collaboration.

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “ስቴም” ማዕከል በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ልኡካን ተጎበኘ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች ስርጭት ተካሄደ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

“በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና ይጫወታሉ!”ዶ/ር ታምራት በየነ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

በዛሬው እለትም የተሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ለአርሶ አደሮች ተሰራጩ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

ለመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባለሙያዎች ተግባር ተኮር ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የመምህራንን የምርምር ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያግዝ ስልጠና ተሰጠ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

የተሻሻሉ የእንሰት ዝርያዎች ስርጭት ተካሄደ

Top News

ዲ.ዩ መጋቢት 11/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ሆስፒታል አዘጋጅነት የምርምር ደረጃን የሚያሳይ የጥናትና ምርምር መረጃ አያያዝና አስተዳደር (Research Data management) እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አውድ በጤናው ዘርፍ ያሉ መርሆዎችን በተመለከተ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ትዝአለኝ ተስፋዬ፤ ኮሌጁ ከጀርመን ግሬፍስዋልድ ዩኒቨርሰቲ (Greifswald) ሁለት ተመራማሪዎች ጋር በተደረገ መግባባት በራሳቸው ፈቃድ በምርምር መረጃ አስተዳደር እና በጤናው ዘርፍ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አውዳዊ መርሆዎች ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
ስልጠናው በጤና የምርምር ዘርፍ ቴክኖሎጂ የደረሰበትን ደረጃ የሚያሳይ መሆኑን ጠቅሰው ለሁሉም ትምህርት ክፍል መምህራን እንዲሁም ከሦስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች እስከ ጀማሪ ተመራማሪዎች ድረስ ላሉ የአካዳሚክ ስታፎች እየተሰጠ እንደሚገኝ አያይዘው ገልጸዋል።
አቶ ትዝአለኝ አክለውም፤ ከጀርመኑ ግሬፍስዋልድ ዩኒቨርሲቲ የመጡ ተመራማሪዎች ምርምር የሚያካሂዱበት ማዕከል ስላላቸው ይህንን የህክምና ማዕከል ከኛ ሆስፒታል ጋር ለማስተሳሰር ፋይዳ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል።
ዶ/ር አትንኩት አላምረው፣ በጀርመን ሀገር ግሬፍስዋልድ ዩኒቨርሲቲ “Post Doctoral ተመራማሪ፣ በጥናትና ምርምር መረጃ አያያዝና አስተዳደር ዙሪያ ስልጠና እየሰጡ ያሉ ሲሆን፣ አቶ ኪሩቤል ብሩክ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪ ሲሆኑ በሰው የሰራሽ አስተውሎት በጤናው ዘርፍ በሚል ርዕስ ስልጠና እንደሚሰጡ ለማወቅ ተችሏል።
በስልጠናው ከ20 በላይ የሚሆኑ መምህራን፣ ተመራማሪዎች እንዲሁም የ3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et

gtadmin