Dilla University

News
Dilla University Hosts 14th Annual National Research Conference

Dilla University Hosts 14th Annual National Research Conference

Upcoming Event: 14th DU Annual National Research Conference

Upcoming Event: 14th DU Annual National Research Conference

Training Provided on Research Ethics and Integrity

Training Provided on Research Ethics and Integrity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

Call For Papers

Call For Papers

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Green University, Sustainable Future

ዲ.ዩ፤ ነሐሴ 11/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ከ ጂ አይ ዜድ (GIZ) ጋር በመተባበር ላዘጋጀው የአራተኛ ዙር የግብርና ባለሙያዎች የክረምት ስልጠና ሰልጣኞች አቀባበልና ገለጻ አድርጓል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዋና ዳሬክተር አለሙ ደሳ (ዶ/ር)፤ ለሰልጣኞች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው፤ አባቶቻችን ቡናን በማምረት የታወቁ ቢሆኑም ምርቱና ውጤቱ ከድካማቸው ጋር የሚጣጣም እንዳልነበር ጠቅሰው ይህ ደግሞ ዘርፉ በዕውቀት ባለመመራቱ እንደሆነ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በቡና ምርት በዓለም 5ተኛ ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃ ላይ የምትቀመጥ መሆኑን ያነሱት ዶ/ር አለሙ፤ ከቡና ምርት ማግኘት የነበረባትን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በሚፈለገው መጠን አለማግኘቷን አያይዘው ተናግረዋል።

ዶ/ር አለሙ አክለውም፤ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም ጭምር ለዘርፉ የተሰጠው ትኩረት አናሳ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ ረገድ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ስልጠናዎችን በመስጠት ጭምር የተሻለ መሆኑን አንስተዋል። አሁንም ከጂ አይ ዜድ ጋር በመተባበር የክረምት የስልጠና መርሐ ግብር ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ኘሬዝዳንት ልዩ ረዳት ዶ/ር አለማየሁ አካሉ በበኩላቸው፤ ቡና ለኢትዮጵያ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ፖለቲካዊ ፋይዳ ያለው እስትራቴጂክ ሰብል መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህን አረንጓዴ ወርቅ የሆነ ሐብታችንን ለማስጠበቅ ውጤቱ የተሻለ እንዲሆን የዲላ ዩኒቨርሲቲ በሁለተኛ ዲግሪ ከማስተማር ጀምሮ የተለያዩ ስልጠናዎችን በመስጠት በዘርፉ ከፍተኛ ስራ እየሰራ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም የስልጠና ኦፊሰር የሆኑት መምህርና ተመራማሪ ኩምሳ ወ/ጊዮርጊስ፤ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማስቀጠል ዘርፉ ልዩ ትኩረት የሚያስፈልገው እንደመሆኑ መጠን ለዚህ ስልጠና ሰፊ ትኩረት በመስጠትና ሞጅሎችን በማዘጋጀት ስልጠናውን ለመስጠት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ቡና 40 በመቶ በማሳ ላይ እንዲሁም 60 በመቶ ከተለቀመ በኋላ በሚኖሩ የአያያዝ ጉድለቶች ጥራቱን ሊያጣ እንደሚችል የገለጹት ተመራማሪው፤ ስልጠናው ሰልጣኞች ከዚህ በፊት ከነበራቸው የተሻለ እውቀትና ግንዛቤ እንዲያገኙ እንደሚረዳቸው ገልጸዋል።

ዲላ፤

የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ

የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

FB: https://www.facebook.com/Du.edu.et

Telegram:https://t.me/dprd9

website: https://www.du.edu.et

Email: https://www.pirdir@du.edu.et