ዲዩ፦ ነሐሴ 01/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከተቆረቆረበት ጀምሮ በመስራችነት ከተቀጠሩ ጥቂት መምህራን ውስጥ አንዱ ሆኑት መምህር ተሰማ አያሌው ብዙዎች እንደሚሉት- ተሴ ከቅጥር እስከ ጡረታ በታማኝነት አገልግለዋል።
ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ሃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ ሲሆን የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች ጭምር ያስተማሩ እና በርካታ ምሩቃንን ያፈሩ ተማሪዎቻቸው እየተዝናኑ ሒሳብን እንዲማሩ የሚያደርጉ ተወዳጅ የሒሳብ መምህር ናቸው። ከዚህም ባሻገር በጡረታ እስከተሰናበቱበት ድረስ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በሚካሄዱ ስብሰባዎች ሃሳባቸውን ፊት ለፊት በማቅረብ የሚታወቁ እና በሚያነሷቸው በርካታ ጉዳዮች በተቋሙ ሰራተኞች ዘንድ የሚወደዱ ናቸው።
መምህር ተሰማ አያሌው ከዚህ ቀደም በርካታ ምርቃቶችን የተመረቅኩ ሲሆን እንደዛሬው ቀን ግን ደስ ያለኝ ቀን የለም፤ በርካታ መስዋዕትነትን በከፈልኩለት ዲላ ዩኒቨርሲቲ በህይወት እያለሁ ይህን በመሰለ ክብር በመሸኘቴ በጣም ደስተኛ ነኝ በማለት የተሰማቸውን ደስታ ገልጸውልናል። በተደረገላቸው የክብር ሽኝትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ተሴ ከቅጥር እስከ ጡረታ ላበረከትከው ከፍተኛ አገልግሎት እናመሰግናለን።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
ለወቅታዊ መረጃዎች
Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://t.me/dprd9
website: https://www.du.edu.et
Email: pirdir@du.edu.et