Dilla University

News
Training Provided on Research Ethics and Integrity

Training Provided on Research Ethics and Integrity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

Call For Papers

Call For Papers

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ ሰኔ 1/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የዕፅዋት ጥበቃና ኢኮቱሪዝም ማዕከል አዘጋጅነት “መሬትን መልሶ ማልማት፣ በረሃማነትንና ድርቅን መቋቋም” በሚል መሪ ሃሳብ በአለም አቀፍ ደረጃ ለ51ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደግሞ ለ31ኛ ጊዜ የአካባቢ ቀን በተለያዩ ኩነቶች ተከብሮ ውሏል።
ሀብታሙ ተመስገን (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት፤ የአካባቢ ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ ከሚከበሩ ቀናት አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፤ ቀኑን በማክበር የተራቆተ አካባቢን ማህበረሰብን በማሳተፍ መለወጥ እንደሚቻል፣ የተራቆቱ መሬቶችን መልሰው እንዲያገግሙ በማድረግ አደጋ እንዳይደርስ ብሎም በአለም ደረጃ እየጨመረ ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ እንዲቀንስ በማድረግ አስተዋጽኦ ማበርከት እንደሚቻል ገልፀዋል።
ታሊሞስ ሴታ (ዶ/ር፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የዕፅዋት ጥበቃና ኢኮቱሪዝም ማዕከል ዳይሬክተር በበኩላቸው፤ አካባቢያችንን እንጠብቅ በሚል በየአመቱ ግንዛቤ ለመፍጠር የሚደረግ ፕሮግራም መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህንን መሠረት በማድረግ በዩኒቨርሲቲያችን ላይ ከሚሰሩ የምርምር ማዕከላት አንዱ በሆነው የዕፅዋትና ኢኮቱሪዝም ማዕከል ይህን ቀን ለማስታወስ የተዘጋጀ ፕሮግራም ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ጌታሁን ሀይሌ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ ተፈጥሮ ሀብት መምህርና ተመራማሪ፤ የአለም አቀፍ የአካባቢ ቀን የተራቆተ መሬት መልሶ እንዲያገግም በማድረግ በርሃማነት እና ድርቅን የሚቋቋም አካባቢና ማህበረሰብ መፍጠር (Land restoration, desertification and drought resilience) በተመለከተ የውይይት መነሻ ሃሳብ ጽሁፍ አቅበው በመድረኩ ተሳታፊዎች ላይ ውይይትና የሀሳብ ልውውጥ ተደርጓል።
ከፕሮግራሙ ተሳታፊዎች መካከል የዲላ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ትምህርት ክፍል 4ኛ ዓመት ተማሪ ይታያል መኳንት በሰጠን አስተያየት፤ ህብረተሰቡ ያለውን የተፈጥሮ ሀብቱን ለመጠቀም፣ የጠፋውን ለመተካትና ለወደፊት ደግሞ ምን ያህል ቀጣይነት እንዲኖረው ለማድረግ ችግኞችን ከተከልን በኋላ ምን ያህል እንክብካቤ እየሰጠናቸው እንደሆነ ግንዛቤ ያገኘሁበት ነው ብሏል፡፡
በፕሮግራሙ በጌዴኦ ዞን የሚገኙ የመንግስት እና የግል ት/ቤቶች፣ መምህራን ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተገኙ ሲሆን በተፈጥሮ ሀብት አያያዝ ትምህርት ክፍል ስለ አከባቢ ጥበቃ የግንዛቤ ፈጠራ ስራ ተሰርቷል። ከዚህም በተጨማሪ የአካባቢ ክበብ አባላት የኪነጥበብና የስነጽሁፍ ስራዎችን ያቀረቡ ሲሆን አረንጓዴ ክለብም ተመስርቷል። በፕሮግራሙ መዝጊያም ተሳታፊዎች ሀገር በቀል ችግኞችን በመትከል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et