Dilla University

News
Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Dilla University signed MOU with Nanjing University to work in partnership

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call for Application: Workshop on Direct Marketing atHSWT & HdbL – Germany

Call For Papers

Call For Papers

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ ግንቦት 8/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አዘጋጅነት ለሁሉም ኮሌጅ ዲኖች፣ ምክትል ዲኖች፣ እንዲሁም ለትምህርት ክፍል ኃላፊዎች በአጠቃላይ የኢንፎርሜሽን ማኔጅመንት ሲስተም ISIMS (Integrated Student Information Management System) ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
አቶ ዮናስ ተጠምቀ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳት ልዩ ረዳት፤ በተለይ በአካዳሚክ ዘርፍ የወረቀት ንክኪን ለመቀነስና ሲስተሙን ለማጠናከር በኮሌጅ ደረጃ ያሉ ዲኖች፣ ም/ዲኖች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ከሲስተሙ ጋር ማላመድና ወደ ስራ በማስገባት በሙሉ አቅም መጠቀምን መሠረት ያደረገ ስልጠና እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
አቶ ዮናስ አክለውም ዲጂታል ሲስተሞችን መጠቀም አገልግሎትን ከማቀላጠፍ አንጻር ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ በቀጣይም ለአካዳሚክ አድቫይዘሮች እንዲሁም ለሁሉም መምህራን ስልጠናውን በመስጠት አገልግሎቱን በላቀ ሁኔታ መጠቀም እንዲቻል የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ማቲዎስ ሀብቴ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር በበኩላቸው፤ ከሁለት ዓመታት በፊት ሲስተሙን ወደ ስራ ለማስገባት እንደተሞከረ እና በዋናነት የአካዳሚክ ፕሮግራሞች እና የአካዳሚክ ዘርፍ ላይ ያሉ ስራዎችን አውቶሜት የማድረግ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸው፤ ይህንን ሲስተም ሙሉ በሙሉ በአካዳሚክ ፕሮግራም ስር የሚካሄዱ ስራዎችን ወደ ዲጂታል ሲስተም እንዲገባ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ደረጃ አየለ፣ በዩኒቨርሲቲው የቅድመ ምረቃና ድህረ ምረቃ ፕሮግራም ኦፊሰር፤ ስልጠናው የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ISIMS ላይ ያለውን ክፍተት ለመለየትና አጠቃላይ አካዳሚክ ዘርፉን በማዘመን ወደ ሲስተም ለማስገባት ያለመ ስልጠና እንደሆነ ገልፀዋል።
ከሰልጣኞች መካከል ከትምህርትና ስነ ባህሪ ተቋም ከካሪኩለም ኢንስትራክሽናል ሱፐርቪዥን ትምህርት ክፍል ኃላፊ፣ መምህርት ኤልሳቤጥ ጊንዶ፤ ስልጠናው ለሁሉም ተቋም የሚያስፈልግ የመረጃ አያያዝ ዘዴን የተመለከተና መረጃዎችን በተቀላጠፈ መልኩ የማደራጀት፣ የተማሪዎችንም ሆነ የስታፍ መረጃዎችን ጊዜና ቦታ ሳይገድበን ሲስተም ላይ የመጫንና የማጋራት ስራ እንድንሰራ የሚያስችል አስፈላጊና ወሳኝ ስልጠና ነበር ሲሉ ገልጸውልናል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


Facebook:https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et