Dilla University

News
Training Provided on Research Ethics and Integrity

Training Provided on Research Ethics and Integrity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

Call For Papers

Call For Papers

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 16/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ም)፦ በተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ (Applied Science University) ስትራቴጂክ ማኔጅመንት ዙሪያ ለዩኒቨርሲቲው አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ችሮታው አየለ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በስልጠናው ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፤ ስልጠናው ለዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል አባላት በሙሉ የሚሰጥና የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት የራሳቸውን አስተዋፅኦ ሊያበረክቱበት የሚገባ አስፈላጊ ስልጠና መሆኑን ጠቁመው፤ በአገራችን የትምህርት ስልጠና ፍኖተ ካርታ ዙሪያ ጥናት ተካሂዶ ዩኒቨርሲቲዎች በተልዕኮ ተለይተውና የትኩረት አቅጣጫ ተቀምጦላቸው በዚህ መሠረት ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ (UAS) በመሆኑ ትኩረት በተደረገባቸው በግብርና፣ ተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ፣ በጤናና በመምህራን ትምህርት በስፋት ትኩረት በማድረግ ዩኒቨርሲቲው ለሚሰራው ስራ ስልጠናው አሰፈላጊ በመሆኑ ሁሉም የአስተዳደር ካውንስል አባላት ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ውጤታማ ስልጠና እንዲሆን መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አብዱ ሐሰን (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የልየታና ትኩረት መስክ ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር፤ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ታሪክ፣ አሁን ያለው ቁመናና ለቀጣይ ያለውን እቅድ፣ የተልዕኮ የልየታና የትኩረት አቅጣጫ ምንነት ፋይዳ በተመለከተ የመነሻ ፅሑፍ አቅርበዋል።
ጌታነህ ሞሱ (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የልየታና ትኩረት መስክ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በበኩላቸው፤ የተግባር ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ ትራቴጂክ፣ ዓላማዎች እና ምክንያቶች፣ ተልእኮዎች፣ የመመሪያ መርሆዎች እንዲሁም የተግባር ዩኒቨርሲቲ ባህሪያት ዙሪያ ገለጻ ሰጥተዋል።
ስልጠናው ስትራቴጅካዊ አስተዳደር፣ የተግባር ተኮር ማስተማር ሂደቶች፣ የኢንዱስትሪ ትስስር፣ የሥራ ፈጠራና የውጭ ንግድ፣ ሥራ ፈጣሪነት፣ ምርምር፣ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር፣ የማህበረሰብ ተሳትፎና አጋርነት ወዘተ በሚሉ ጉዳዮች ዙሪያ ለቀጣይ አራት ቀናት እንደሚሰጥ ተገልጿል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት


ለወቅታዊ መረጃዎች
Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://t.me/dprd9
website: https://www.du.edu.et
Email: pirdir@du.edu.et