Dilla University

News

8th International Conference on Mathematics and Mathematics Education

Dilla University Hosts 14th Annual National Research Conference

Dilla University Hosts 14th Annual National Research Conference

Upcoming Event: 14th DU Annual National Research Conference

Upcoming Event: 14th DU Annual National Research Conference

Training Provided on Research Ethics and Integrity

Training Provided on Research Ethics and Integrity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

Call For Papers

Call For Papers

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ ታሕሳስ 19/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በጌዴኦ ዞን ከሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተወጣጡ የኬሚስትሪ መምህራን በኬሚስትሪ ቨርቹዋል ቤተ ሙከራ ዙርያ ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።

አቶ ተካልኝ ታደሰ፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር፣ ለትምህርት ጥራት መሻሻል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብ እንደሚፈልግ ጠቁመው፤ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በዞኑ ከጊዜ ወደ ጊዜ የተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍን የሚመርጡ ተማሪዎች ቁጥር እየቀነሰ መምጣቱን አንስተዋል። ይህን ክፍተት ለማስተካከልና በአጠቃላይ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ዲላ ዩኒቨርሲቲ የበኩሉን ሚና ለመወጣት የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ መሆኑንም አስረድተዋል።

ስልጠናውን የወሰዱት መምህራን ያገኙትን እውቀትና ልምድ ወደየትምህርት ቤታቸው ሲመለሱ ተግባር ላይ እንዲያውሉት የአደራ መልእክታቸውን አያይዘው አስተላልፈዋል።

አቶ አለማየሁ ገናታ፣ የጮርሶ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ በበኩላቸው፤ ስልጠናው የዘመኑን ቴክኖሎጂ መሰረት ያደረገ በመሆኑ በትምህርት ቤቶችና በወረዳው የነበረው የቤተ-ሙከራ የግብዓት ችግር በማቃለል የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል። ሰልጣኞችም ከስልጠናው ባገኙት እውቀት በየትምህርት ቤቶች በሚገኙ ኮምፒውተሮች የተለያዩ ሶፍትዌሮችን በመጫን የተለያዩ ሙከራዎችን ለመስራት የሚያስችል አቅም እንደተፈጠረላቸው አውስተው ዲላ ዩኒቨርሲቲ እንዲህ ያሉ ስልጠናዎችን በመስጠት እያደረገ ያለውን እገዛ አመስግነው መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

አቶ ብሩህ ተስፋሁን፣ በዩኒቨርሲቲው ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት የአጫጭር ስልጠናዎች አስተባባሪ የማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ከሚሰራቸው አንኳር ተግባራት አንዱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት መሆኑን አስታውሰው፤ በኬሚስትሪ ቨርቹዋል ቤተ ሙከራ በቂ እውቀትና ልምድ ባላቸው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኬሚስትሪ መምህራን ለሶስት ቀናት ሲሰጥ በነበረው ስልጠና ከጌዴኦ ዞን ጮርሶ ክላስተር ከሚገኙ ስድስት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ የኬሚስትሪ መምህራን ተሳታፊ መሆናቸውን አሳውቀዋል።

አቶ ብሩህ አክለው፤ ስልጠናውን አሳታፊና ተግባር ተኮር በማድረግ ሰልጣኝ መምህራን ወደየትምህርት ቤታቸው ሲመለሱ ያገኙትን እውቀትና ልምድ ለተማሪዎቻቸው የሚያስተምሩበት የሙከራ እቅድ ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ስልጠናውን ከወሰዱ መምህራን መካከል ትታይ አሸብር እና ጥበቡ ሰለሞን በሰጡን አስተያየት፤ ተማሪዎችን የተለያዩ ሙከራዎችን ለማሰራት ከኬሚካል ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ የግብዓት እጥረት ይገጥማቸው እንደነበር ጠቅሰው፤ አሁን በወሰዱት ስልጠና በትምህርት ቤታቸው የሚገኙ ኮምፒውተሮች ላይ የኬሚስትሪ ቨርቹዋል ቤተ ሙከራ ሶፍትዌርን በመጫን ስርዓተ ትምህርቱ የሚያዘውን የተግባር ትምህርት ሁሉ ተማሪዎቻቸውን ለማሰራት የሚያስችል እውቀትና ክህሎት መያዛቸውን ተናግረዋል።

የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

ዲላ ዩኒቨርሲቲ

የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ

Telegram: https://t.me/dprd9

Email: pirdir@du.edu.et

p.o.box: 419

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *