የማህበረሰብ አቀፍ አጋርነት ፕሮጀክት ትልም ግምገማ ተካሄደ

ዲ.ዩ፤ ግንቦት 14/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት ከጌዴኦ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመሆን የቀረጸውንና ለ4 ዓመት ይቆያል የተባለውን የማህበረሰብ አቀፍ አጋርነት ፕሮጀክት ትልም ግምገማ) (Community Engagemeng Project Proposal Defense) አካሂዷል።

Read more

የ4ተኛው ሳምንት የላብራቶሪ ኤግዚብሽን ተካሄደ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 20/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ 4ተኛውን ሳምንት የላብራቶሪ ኤግዚብሽን አካሂዷል።
አንተነህ ወጋሶ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ዲን በወቅቱ እንደገለጹት፤ የላብራቶሪ ኤግዚብሽኑ ላለፉት ሦስት ተከታታይ ሳምንታት እየተካሄደ መቀጠሉን ገልጸው፤ በባለፈው ሳምንት በኮሌጁ በተያዘው ማንዋል መሰረት በኤግዚብሽኑ የኮሌጁ የውሃ ሃብት እና መስኖ ምህንድስና ት/ቤት ላብራቶሪዎቻቸውን ማቅረባቸውን ገልጸዋል።

Read more

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የላብራቶሪ ኤግዚብሽን አካሄደ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 05/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ 2ተኛውን ሳምንት የላብራቶሪ ኤግዚብሽን አካሂዷል።
አቶ ዮናስ ተጠምቀ፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለጹት፤ ላብራቶሪዎች ከፍተኛ በጀት ወጥቶባቸው የተገነቡ እንደመሆናቸው መጠን አጠቃላይ የኮሌጁ መምህራንና የላብራቶሪ አሲስታንቶች ላብራቶሪዎችን በሚገባ ተጠቅመው ከመማር ማስተማሩ ባለፈ ለተቋሙ የገቢ ምንጭነትም ጭምር እንዲሆኑ ማስቻል እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

Read more

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በህክምናና ጤና ሳይንስ፣ በኪነ-ህንፃ ምህንድስና እና በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ

ዲ.ዩ፤ የካቲት 16/2016ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና (Medicine) ትምህርት ክፍልን ጨምሮ በሌሎች አምስት ትምህርት ክፍሎች፣ ከቴክኖሎጂና ምህንድስና ኮሌጅ በኪነ-ህንፃ ምህንድስና (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል፣ እንዲሁም በተለያዩ የሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በዛሬው እለት አስመርቋል።

Read more

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከስፔኑ የካታሎኒያን ግዛት ጋቫ የስፖርት ልማት ጋራ የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራረመ፤

ዲ.ዩ፤ የካቲት 03/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ እና የስፔኑ የካታሎኒያን ግዛት ጋቫ የስፖርት ልማት በስፖርት ዘርፍ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸው ተገልጿል።

Read more

የጌዴኦ ብሔር የቋንቋና ባህል ሲምፖዚየም ተካሄደ፤

ዲ.ዩ፤ የካቲት 1/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ እና የጌዴኦ ዞን አስተዳደር በትብብር ያዘጋጁት “ክብር ለአካባቢ ጥበቃ ጀግኖቻችን የጌዴኦ ማሕበረሰብ” በሚል መሪ ቃል የጌዴኦ ብሔር የቋንቋና ባህል- ዳራሮ ሲምፖዚየም ተካሂዷል።

Read more