በሰላም እሴቶች ግንባታ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 27/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት እና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ከጌዴኦ ዞን መምሪያ፣ ከምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ እና ከሲዳማ ክልል ዳራ ወረዳዎች ለተወጣጡ የሰላምና ፀጥታ ባለሙያዎች በሰላም እሴቶች ግንባታ ላይ ያተኮረ ስልጠና ለተከታታይ ሶስት ቀናት ተሰጥቷል።

Read more

የ4ተኛው ሳምንት የላብራቶሪ ኤግዚብሽን ተካሄደ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 20/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ 4ተኛውን ሳምንት የላብራቶሪ ኤግዚብሽን አካሂዷል።
አንተነህ ወጋሶ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ ዲን በወቅቱ እንደገለጹት፤ የላብራቶሪ ኤግዚብሽኑ ላለፉት ሦስት ተከታታይ ሳምንታት እየተካሄደ መቀጠሉን ገልጸው፤ በባለፈው ሳምንት በኮሌጁ በተያዘው ማንዋል መሰረት በኤግዚብሽኑ የኮሌጁ የውሃ ሃብት እና መስኖ ምህንድስና ት/ቤት ላብራቶሪዎቻቸውን ማቅረባቸውን ገልጸዋል።

Read more

13ኛው ዓመታዊ አገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተካሄደ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 19/2016 (ህ.ዓ.ግ)፦ 13ኛው አገር አቀፍ ዓመታዊ የምርምር ጉበኤ“ምርምር ለማህበረሰብ ለውጥ” በሚል ዋና ጭብጥ
በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል። የዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት እና የምርምር፣ ህትመት፣ ሥነ ምግባርና ሥርፀት ዳይሬክቶሬት ጉባኤውን አሰናድተውታል።

Read more

ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተከብሮ ዋለ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 14/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ በሴቶች፣ ህፃናት እና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን “ሴቶችን እናብቃ፣ ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ሃሳብ ከዩኒቨርሲቲው አንጋፋ ሴት መምህራን ጋር የልምድ ልውውጥ በማድረግ በዓሉን በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብሮ ውሏል። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ113ኛ ጊዜ እንዲሁም በሀገራችን ደግሞ ለ48ኛ ጊዜ ተከብሮ መዋሉ ታውቋል።

Read more

በመረጃ አስተዳደር እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል

ዲ.ዩ መጋቢት 11/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ሆስፒታል አዘጋጅነት የምርምር ደረጃን የሚያሳይ የጥናትና ምርምር መረጃ አያያዝና አስተዳደር (Research Data management) እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) አውድ በጤናው ዘርፍ ያሉ መርሆዎችን በተመለከተ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

Read more