ለክረምት መርሃ ግብር 5ኛ ዓመት #ግብርናናተፈጥሮሃብት ኮሌጅ ተማሪዎች
ትምህርታችሁን በእንስሳት ሳይንስ፣ በእንስሳት ጤና እና በእጸዋት ሳይንስ በክረምት መርሃ ግብር እየተከታተላችሁ ያላችሁ የ5ኛ ዓመት ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚከናወነው ጥር 15 እና 16/2016 ዓ.ም መሆኑን እንገልጻለን።
ትምህርታችሁን በእንስሳት ሳይንስ፣ በእንስሳት ጤና እና በእጸዋት ሳይንስ በክረምት መርሃ ግብር እየተከታተላችሁ ያላችሁ የ5ኛ ዓመት ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ የሚከናወነው ጥር 15 እና 16/2016 ዓ.ም መሆኑን እንገልጻለን።
በሪሜዲያል ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ
በ2016 ዓ.ም ዲላ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ወደ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የምትገቡበትና የምትመዘገቡበት ቀን ጥር 23 እና 24/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ በተገለጸው ቀን ዲላ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ (ኦዳያኣ ካምፓስ) በሚገኘው ሬጂስትራር ጽ/ቤት በአካል ተገኝታችሁ እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን፡፡
የዲላ ዩኒቨርሲቲ #የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት በዘርፉ ባሉት ክፍት የኃላፊነት ቦታዎች መምህራንን አወዳድሮ መመደብ ይፈልጋል። በመሆኑም ዘርፉ ባሉት ክፍት የኃላፊነት ቦታዎች መወዳደር የምትፈልጉ መምህራን ከዚህ ማስታወቂያ ጋር አባሪ ተደርጎ በቀረበው መሰረት እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ #የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ዘርፍ ባሉት ክፍት የስራ ቦታዎች መምህራንን አወዳድሮ የተለያዩ ኦፈሰሮችና አስተባባሪዎችን መመደብ ይፈልጋል።
ዲ.ዩ፤ ጥር 3/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ከኢትዮጵያ ሴት ቡና አልሚ ገበሬዎች ማሕበር (Women in coffee Ethiopia) ጋር በመተባበር በቡና ምርት ጥራት ዙሪያ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቋል።
ዲ.ዩ፤ ጥር 02/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስቴም ማዕከል በጌዴኦ ዞን በሚገኙ ትምህርት ቤቶች፦ ገደብ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት፣ ቀዲዳ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እንዲሁም አዳሜ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የሳይንስ ኤግዚቢሽንና ፓናል ውይይት አካሂዷል።
ዲ.ዩ፤ ጥር 1/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት ጥር 01/2016 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ተገቢውን መስፈርት አሟልተው ተገኝተዋል ያላቸውን አምስት መምህራን የተባባሪ ፕሮፌሰርነት (Associate professor) ማዕረግ አካዳሚክ ደረጃ ዕድገት (promotion) ሰጥቷል።
ዲ.ዩ፤ ጥር 1/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ከኢትዮጵያ ሴቶች ቡና አልሚ ገበሬዎች ማህበር (Women in coffee Ethiopia ) ጋር በመተባበር በቡና ምርት ዙሪያ ለሴት ቡና አልሚ ገበሬዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው።
ዲ.ዩ፤ ታህሳስ 28/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ አጠቃላይ ሆስፒታል አስተዳደር ከህሙማና ሰራተኞች ጋር የገና በዓልን በድምቀት አክብረዋል።
ዲ.ዩ፣ ታህሳስ 25/2016 ዓ.ም. (ህ.ዓ.ግ)፣ የመቻቻልና የአብሮነት ቀንን ምክኒያት በማድረግ በስፖርት ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህራን የተመራ የማስ ስፖርት እንቅስቃሴ ከንጋቱ 12:00 ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ሁለገብ ስታዲየም ተከናውኗል።