ለይርጋጨፌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ድጋፍ ተደረገ፤
ዲ.ዩ፣ ጥር 10/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት እና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለይርጋጨፌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህክምና ባለሙያዎች የህፃናት ድንገተኛ ህክምናን፣ የጨቅላ ህፃናት እንክብካቤን እና የምግብ እጥረት ያለባቸው ህፃናት የህክምና አገልግሎትን ለማሻሻል የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል።