በቆልማማ እግር (Clubfoot) ልየታና የህክምና አገልግሎት ድጋፍ አሰጣጥ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ
ዲ.ዩ፤ የካቲት 02/2016 ዓ.ም. (ህ.ዓ.ግ)፦ “ሆፕ ወክስ” (HOPE WALKS) በጎ አድራጎት ድርጅት ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤና እና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ አጠቃላይ ሆስፒታል በመገኘት እግራቸው ቆልማማ በሆነ ታካሚዎች ዙሪያ ከጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ ለተወጣጡ 100 ለሚሆኑ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ስልጠና የሰጠ ሲሆን በሆስፒታሉ ቆልማማ እግር ላላቸው ታካሚ ህፃናት የህክምና አገልግሎት ድጋፍ አድርጓል፡፡
Read more