በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ
ዲ.ዩ፤ የካቲት 04/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክቶሬት ከጌዴኦ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች፣ ከምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ እና ከሲዳማ ክልል ዳራ ወረዳ ለተወጣጡ የማዘጋጃ ቤት እና የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች በተቀናጀ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ዲ.ዩ፤ የካቲት 04/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክቶሬት ከጌዴኦ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች፣ ከምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ እና ከሲዳማ ክልል ዳራ ወረዳ ለተወጣጡ የማዘጋጃ ቤት እና የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች በተቀናጀ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ዲ.ዩ፤ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ሆስፒታል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን “ሴቶችን እናብቃ፣ ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ሃሳብ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብሮ ውሏል። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ113ኛ ጊዜ እንዲሁም በሀገራችን ደግሞ ለ48ኛ ጊዜ ተከብሯል።
ዲ.ዩ የካቲት 30/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ድጋፍ ማዕከል ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በድምጽ አማካኝነት በሚሰጥ ትዕዛዝ ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችልና ለአይነስውራን ተስማሚ የሆነ (Job Access With Speech) የኮምፒውተር መተግበሪያ እና የብሬል ማንበብና መጻፍ ክህሎት ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
የካቲት 28/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ) ፦ በቡና ዘርፍ ላይ አበረታች ውጤት ለማምጣት የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ በመተባበር ውጤታማ ስራ መስራት እንደሚችሉ የገለጹት “የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ለኢትዮጵያ ቡና ኢንዱስትሪ ሽግግር” በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ ባለው 4ኛው የቡና ሲምፖዚየም ላይ ንግግር ያደረጉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ናቸው።
The Role of Stakeholders’ Collaboration in Transforming Ethiopia’s Coffee Industry.
The Fourth National Coffee Symposium is happening now at Capital International Hotel, Adiss Ababa.
ዲ.ዩ፤ የካቲት 26/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡና ማህበር ጋር በመተባበር “የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ለኢትዮጵያ የቡና ኢንዱስትሪ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል አራተኛውን ሀገር አቀፍ የቡና ሲምፖዚየም የፊታችን ሐሙስ የካቲት 28/2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ካፒታል ኢንተርናሽናል ሆቴል ያካሂዳል።
ዲ.ዩ፤ የካቲት 19/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማሕበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብዕ ኮሌጅ ለስምንት የሥነ-ዜጋና ሥነ ምግባር የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች ላፕቶፕ ኮምፒዩተር በስጦታ አበርክቷል።
ዲ.ዩ፤ የካቲት 17/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በዲላ ከተማ ለሚገኙ አካል ጉዳተኛ ማሕበራት አባላት በፕሮጀክት ዕቅድ አዘገጃጀት ዙርያ ስልጠና ተሰጥቷል።
ዲ.ዩ፤ የካቲት 17/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በቡና አዘገጃጀትና ጥራት ምርመራ ላይ በጌዴኦ ዞን ለሚገኙ ሕብረት ስራ ማሕበራት የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።
ዲ.ዩ፤ የካቲት 16/2016ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የህክምና (Medicine) ትምህርት ክፍልን ጨምሮ በሌሎች አምስት ትምህርት ክፍሎች፣ ከቴክኖሎጂና ምህንድስና ኮሌጅ በኪነ-ህንፃ ምህንድስና (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል፣ እንዲሁም በተለያዩ የሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በዛሬው እለት አስመርቋል።