“በሁለም ዘርፍ የበቁ ሴቶች አለምን ያበቃሉ” መምህርት ኤደን አሸናፊ
ዲ.ዩ፤ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ሆስፒታል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን “ሴቶችን እናብቃ፣ ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ሃሳብ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብሮ ውሏል። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ113ኛ ጊዜ እንዲሁም በሀገራችን ደግሞ ለ48ኛ ጊዜ ተከብሯል።