በምርምር የበለጸገ የአፕል ችግኝ ለአርሶ አደሮች ተሰራጨ

ዲ.ዩ ነሐሴ 20/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ከቡሌና ራጴ ወረዳ ለተወጣጡ አርሶ አደሮች በምርምር የበለፀገ የአኘል ችግኝ ስርጭት አካሂዷል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ተካልኝ ታደሰ፤ ዩኒቨርሲቲው በደጋ ፍራፍሬ ዙሪያ በሰፊው እየሰራ መሆኑን ገልፀው፤ በዋናነት በአኘል ላይ ለረጅም ጊዜ እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ ከቡሌ ወረዳ 8 ቀበሌዎች ከራጴ ወረዳ በተመሳሳይ 8 ቀበሌዎች ለተወጣጡ አርሶ አደሮች የአኘል ችግኝ መሰራጨቱን ተናግረዋል።

Read more

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምር ስልጠና ተቋም ሰልጣኞች የመስክ ስልጠናና ልምድ ልውውጥ አካሄዱ

ዲ.ዩ፤ ነሐሴ 19/12/16 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምር ስልጠና ተቋም በአራተኛ ዙር እያሰለጠናቸው ያሉትን የግብርና ባለሙያዎች በጽንሰ ሐሳብ ደረጃ ሲማሩ የቆዩትን በተግባር የመስክ ምልከታና ልምምድ እንዲያገኙ ማድረጉ ተገልጿል።

Read more

የኢትዮጵያ ግብርና ናሙና ቆጠራ ስልጠና የመክፈቻ ስነ ስርዓት ተካሄደ

ዲ.ዩ፤ ነሐሴ 18/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ከኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በትብብር የተዘጋጀው “የግብርና ቆጠራ ለመረጃ ምሉዕነት” በሚል መሪ ቃል አገር አቀፍ የኢትዮጵያ ግብርና ናሙና ቆጠራ ባለሙያዎች ስልጠና የማስጀመሪያ መርሐ ግብር በዲላ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ተከናውኗል።

Read more

ዲላ ዩኒቨርሲቲ “የምትተክል ሀገር፤ የሚያፀና ትውልድ” በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ

ዲ.ዩ፤ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለው “የምትተክል ሀገር፣ የሚያጸና ትውልድ” የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ ተከላ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በአራቱም ግቢዎች ከማለዳ ጀምሮ ተከናውኗል፡፡

ችሮታው አየለ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዛሬ በሀገር አቀፍ ደረጃ 600 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል እንደ ሀገር እቅድ ተይዞ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀው፤ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብም ይህንን ዕቅድ ለማሳካት በአራቱም ግቢዎች የአረንጓዴ አሻራ የማኖር ስራ ማከናዎናቸውን ገልጸዋል።

Read more

የልዩ የክረምት ስልጠና ተሳታፊ መምህራንና ርዕሰ መምህራን ስልጠና ተጠናቀቀ

ዲ.ዩ፤ ነሐሴ 15/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በክረምት ልዩ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው ስልጠናቸውን ሲከታተሉ ለቆዩ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራንና አመራሮች የማጠቃለያ ፈተና ተሰጥቶ ስልጠናው ተጠናቋል።

Read more