ሀገር በቀል እውቀቶችን በመጠበቅ ለትውልድ ማስተላለፍ እንደሚገባ ተገለጸ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 09/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክቶሬት ከጌዴኦ ዞን፣ ከምዕራብ ጉጂ አባያ ወረዳ እና ከሲዳማ ክልል ዳራ ወረዳ ለተወጣጡ የባህልና ቱሪዝም ባለሙያዎች በሀገር በቀል ዕውቀት ዙሪያ ሰልጠና ሰጥቷል፡፡

Read more

የገበያ ጥናት አሰራርን በተመለከተ ለባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ

መጋቢት 05/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ም)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክቶሬት በጌዴኦ ዞን ለሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች፣ በምዕራብ ጉጂ ዞን ለአባያ ወረዳ እና ለሲዳማ ክልል ዳራ ወረዳ የንግድና ገበያ ልማት ባለሙያዎች በገበያ ጥናት መረጃ አሰባሰብ፣ ትንተናና ስርጭት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ታውቋል።

Read more

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ የላብራቶሪ ኤግዚብሽን አካሄደ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 05/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ኮሌጅ 2ተኛውን ሳምንት የላብራቶሪ ኤግዚብሽን አካሂዷል።
አቶ ዮናስ ተጠምቀ፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር እንደገለጹት፤ ላብራቶሪዎች ከፍተኛ በጀት ወጥቶባቸው የተገነቡ እንደመሆናቸው መጠን አጠቃላይ የኮሌጁ መምህራንና የላብራቶሪ አሲስታንቶች ላብራቶሪዎችን በሚገባ ተጠቅመው ከመማር ማስተማሩ ባለፈ ለተቋሙ የገቢ ምንጭነትም ጭምር እንዲሆኑ ማስቻል እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

Read more

በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፤ የካቲት 04/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎት አጋርነት ዳይሬክቶሬት ከጌዴኦ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች፣ ከምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ እና ከሲዳማ ክልል ዳራ ወረዳ ለተወጣጡ የማዘጋጃ ቤት እና የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች በተቀናጀ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዙሪያ ስልጠና ሰጥቷል፡፡

Read more

“በሁለም ዘርፍ የበቁ ሴቶች አለምን ያበቃሉ” መምህርት ኤደን አሸናፊ

ዲ.ዩ፤ መጋቢት 3/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ሆስፒታል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን “ሴቶችን እናብቃ፣ ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ” በሚል መሪ ሃሳብ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብሮ ውሏል። ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ113ኛ ጊዜ እንዲሁም በሀገራችን ደግሞ ለ48ኛ ጊዜ ተከብሯል።

Read more

አይነስውራን ተማሪዎች ተስማሚ መሠረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና (Jaws) እየተሰጠ ነው

ዲ.ዩ የካቲት 30/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎት ትምህርት ድጋፍ ማዕከል ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በድምጽ አማካኝነት በሚሰጥ ትዕዛዝ ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችልና ለአይነስውራን ተስማሚ የሆነ (Job Access With Speech) የኮምፒውተር መተግበሪያ እና የብሬል ማንበብና መጻፍ ክህሎት ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡

Read more

“በቡና ዘርፍ ላይ አበረታች ውጤት ለማምጣት የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ በመተባበር ውጤታማ ስራ መስራት ይችላሉ” ዶ/ር ችሮታው አየለ።

የካቲት 28/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ) ፦ በቡና ዘርፍ ላይ አበረታች ውጤት ለማምጣት የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ በመተባበር ውጤታማ ስራ መስራት እንደሚችሉ የገለጹት “የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ለኢትዮጵያ ቡና ኢንዱስትሪ ሽግግር” በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ ባለው 4ኛው የቡና ሲምፖዚየም ላይ ንግግር ያደረጉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ናቸው።

Read more

አራተኛው ሀገር አቀፍ የቡና ሲምፖዚየም ሊካሄድ ነው

ዲ.ዩ፤ የካቲት 26/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡና ማህበር ጋር በመተባበር “የባለድርሻ አካላት ቅንጅት ለኢትዮጵያ የቡና ኢንዱስትሪ ሽግግር” በሚል መሪ ቃል አራተኛውን ሀገር አቀፍ የቡና ሲምፖዚየም የፊታችን ሐሙስ የካቲት 28/2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ካፒታል ኢንተርናሽናል ሆቴል ያካሂዳል።

Read more