Dilla University

News

8th International Conference on Mathematics and Mathematics Education

Dilla University Hosts 14th Annual National Research Conference

Dilla University Hosts 14th Annual National Research Conference

Upcoming Event: 14th DU Annual National Research Conference

Upcoming Event: 14th DU Annual National Research Conference

Training Provided on Research Ethics and Integrity

Training Provided on Research Ethics and Integrity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

Call For Papers

Call For Papers

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ ጥር 25/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ (Remedial) መርሃ ግብር ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው ለመጡ ተማሪዎች ገለጻ (Orientation) ተሰጥቷል።
አቶ አማኑኤል ጌካ፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር፤ የ 2016 ዓ.ም የሪሜዲያል መግቢያ መስፈርቱን አሟልታችሁ ወደ ዩኒቨርሲቲያችን የመጣችሁ ተማሪዎች እንኳን ወደ አረንጓዴው ምድር ዲላ ዩኒቨርሲቲ በደህና መጣችሁ በማለት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል
አቶ አማኑኤል አያይዘውም፤ የተማሪዎች አገልግሎት ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ተማሪዎችን ከመቀበል ጀምሮ መሰረታዊ አገልግሎቶችን እንዲያገኙ የተሳካ ስራ ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው በቀጣይ ተማሪዎች በግቢ ቆይታቸው በማስታወቂያ ቦርድ ላይ የሚለጠፉ መልዕክቶችን በንቃት በመከታተል እንዲተገብሩ አደራ ብለዋል።
በዩኒቨርሲቲው የ’ፍሬሽማን’ ፕሮግራም ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ዲን መ/ር መንግስቱ ተሾመ፤ በአቅም ማሻሻያ መርሃ ግብር የተመደቡ ተማሪዎች ከ27/05/16 ዓ.ም ጀምሮ ትምህርት እንደሚጀምሩ ገለጸው፤ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው በሚሰጧቸው የተለያዩ ተከታታይ ምዘናዎች 30 ከመቶ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚሰጠው ፈተና ደግሞ 70 ከመቶ እንደሚያዝላቸው አብራርተዋል።
ከምዘናው በኋላም በድምር ውጤታቸው 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ማምጣት የቻሉ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲው የመጀመሪያ ዓመት (Freshman) ተማሪ ሆነው እንደሚቀጥሉ መ/ር መንግስቱ አክለው ገልፀዋል።
መ/ር መንግስቱ አክለውም የፍሬሽማን ጽ/ቤት በአቅም ማሻሻያ መርሃ ግብር አስተባባሪዎችን በመመደብ የመማር ማስተማር ሂደቱ ውጤታማ እንዲሆን ክትትል እና ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
አስናቀ ይማም (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ዋና ሬጅስትራር በበኩላቸው፤ በዩኒቨርሲቲው ለ 2016 ዓ.ም በአቅም ማሻሻያ መርሃ ግብር 1699 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች እና 1385 የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች፤ በድምሩ 3084 ተማሪዎች መመደባቸውን ገልፀዋል።
አቶ አዲስ ታምሩ፣ የሕግ ትምህርት ክፍል መምህርና የዩኒቨርሲቲው የህግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የዩኒቨርሲቲውን የተማሪዎች የዲሲፒሊን መመሪያ መሰረት በማድረግ ተማሪዎቹ በግቢ ውስጥ ሊከተሏቸው ስለሚገቡ የስነ ምግባር መርሆዎች ገለጻ አድርገዋል።
የማጠቃልያ ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ ነዲ ገቢሳ፣ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ፤ ተማሪዎች በቆይታቸው ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ጠንክረው በመስራት የልጅነት ህልማቸውን እውን ለማድረግ እንዲተጉ አደራ ብለዋል።
ገለጻውን ሲከታተሉ ካገኘናቸው ተማሪዎች መካከል ተማሪ ሄርሜላ አክሊል እና ተማሪ አስማማው ደምሴ፤ ከመጡበት ቀን ጀምሮ በተቋሙ የተደረገላቸው አቀባበል እንዳስደሰታቸው ገልጸው፤ የተደረገላቸው ገለጻ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ሊኖራቸው የሚገባውን ስነምግባር እንዲገነዘቡ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል።
በገለጻው ወቅት የዩኒቨርስቲው አመራሮች፣ ሰራተኞች፣ የተማሪዎች ሕብረት ተወካዮች፣ መምህራን፣ የፀጥታ አካላት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።