የዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተመራማሪዎች በጣሊያን አገር ቱሪን ዩኒቨርሲቲ ጉብኝት አካሄዱ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 10/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፥ በዲላ ዩኒቨርሲቲ እና በጣሊያን አገር የሚገኘው ቱሪን ዩኒቨርሲቲ የጋራ ትብብር ስምምነት አካል የሆነ የመምህራን ጉብኝት ተካሄደ። የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስት መምህራንና ተመራማሪዎች ናቸው ከሚያዚያ 28 እስከ ግንቦት 11/2015 ዓ.ም የሚቆየውን ጉብኝት በቱሪን ዩኒቨርሲቲ እያካሄዱ ያሉት።
እንደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተሰጡት ተልዕኮዎች ውጤታማ ለመሆን አገራዊና ዓለምአቀፋዊ ትብብሮችን ከተለያዩ ተቋማት ጋር እየተፈራረመ ይተገብራል። በጣሊያን አገር ቱሪን ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ያለው የመምህራኑና ተመራማሪዎቹ ጉብኝትና ወይይትም የዚሁ አላማ አካል መሆኑ ነው የተገለፀው።

ለጌዴኦ ዞን ግብርና ባለሙያዎች በ"ጂ.አይ.ኤስ" የመረጃ አሰባሰብ ዙሪያ የክህሎት ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 10/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከጌዴኦ ዞን ጋር በመተባበር በ"ጂ.አይ.ኤስ" (GIS) አጠቃላይ ዲጂታል መረጃ አሰባሰብ ዙሪያ ለዲላ ዙርያ ወረዳ 17 የግብርና ባለሙያዎች የክህሎት ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጥቷል።
በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አለማየሁ አካሉ (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ኘሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ፤ ለምንሰራው ስራ በቂ ክህሎትና እውቀት መታጠቅ በእጅጉ አስፈላጊ በመሆኑ፤ ያለንን እና የጎደለንን ለመለየት ይህ ስልጠና ትልቅ አስተዋጾ አለው ብለዋል።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የሞዴል ፈተና መሰጠት ተጀመረ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 09/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በ"ኦንላይን" የታገዘና ለአገር አቀፍ የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና የሚያዘጋጅ የሞዴል ፈተና መስጠት ጀምሯል።
ማቴዎስ ሀብቴ (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ፤ በመጪው ሐምሌ ወር በመንግስትና የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሀገር አቀፍ ደረጃ ይሰጣል ተብሎ እቅድ የተያዘለትን የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና በዩኒቨርሲቲው በብቃት ለመስጠት ሰፊ ዝግጅት ሲደርግ መቆየቱን ገልጸዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራር ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 04/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ችሮታው አየለ (ዶ/ር) የተመራ ከፍተኛ የአመራር ቡድን በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉ ልዩ ልዩ የመሠረተ ልማት ስራዎችን ጎብኝቷል።
በከፍተኛ አመራሩ ምልከታ መጀመሪያ በኦዳያአ ግቢ እየተሰራ ያለ የዩኒቨርሲቲውን አጠቃላይ ደህንነት፣ የተማሪዎች እና ሰራተኞች አገልግሎት አሰጣጥ የሚመለከቱ ዘርፎችን ደህንነትና መረጃ አያያዝ የሚያዘመንን የአይ.ሲቲ መሰረተ ልማት (Security Operation Center) ተጎብኝቷል።

በጌዴኦ ዞን ኮቾሬ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች በምርምር የለማ የቡና ችግኝ ተሰራጨ

ዲ.ዩ፦ ሚያዝያ 15/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት በጌዴኦ ዞን ኮቾሬ ወረዳ ከ19 ቀበሌዎች ለተውጣጡ አርሶ አደሮች በምርምር የለሙ የቡና ችግኞችን አከፋፍሏል።
ደረጀ ክፍሌ (ዶ/ር) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት፤ ዩኒቨርሲቲው ከአስራ ሦሥት በላይ ለማህበረሰቡ ተደራሽ የሚሆኑ ፕሮጀክቶችን እየሰራ ለማህበረሰብ ግልጋሎት ተደራሽ እያደረገ መሆኑን ገልፀዋል።
ከእነዚህም መካከል በዘንድሮ ዓመት በኮቾሬ ወረዳ ሊሰራጭ ከታቀደው 80 ሺህ የቡና ችግኝ ውስጥ ለሚያዚያ ተከላ የደረሱ 63 ሺህ የቡና ችግኞች ለአርሶ አደሮች እንዲደርሱ መደረጋቸውን ዶ/ር ደረጄ ገልጸዋል።

በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የቡና ችግኝ ተሰራጨ

ዲ.ዩ፦ ሚያዚያ 13/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ አምስት ቀበሌዎች ለተውጣጡ አርሶ አደሮች በምርምር የለሙ የቡና ችግኞችን አሰራጭቷል።
ደረጀ ክፍሌ (ዶ/ር )፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት፤ ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር እና ከምርምር ስራዎች ባለፈ በርከት ያሉ የማህበረሰብ ተደራሽ ፕሮጀክቶችን ለአካባቢው ህብረተሰብ ተጠቃሚነት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

Pages