በዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል የአጥንት ቀዶ ህክምና አገልግሎት በስፋት እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ

ዲ.ዩ፦ የካቲት 10/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል ከትራፊክ አደጋ ጋር ተያይዞ ከሚሰጠው አገልግሎት መካከል በተለይ የአጥንት ቀዶ ህክምና አገልግሎትን በስፋት እየሰጠ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡
ዶ/ር አብይ ብርሃኑ፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል በአጥንት ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት፤ የአጥንት ህክምና በብዛት ድንገተኛ ህክምና ላይ ትኩረት ያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል። ይህም ድንገተኛ ህክምና ከአደጋ ጋር የተያያዙ ህክምና እና ካንሰርን ጨምሮ 'ኢንፌክሽን' እንዲሁም ሌሎች መሰል ህክምናዎች የሚሰጥበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

የጨረታ ማስታወቂያ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች ምግብ ግብአት የሚውሉ፣ ለመማር ማስተማርና ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ግቡዓቶችንና የግንባታ ስራዎችን በግልፅ ጠረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። ጨረታውን መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታህሳስ 10/2015 ዓ.ም ታትሞ በወጣው የጨረታውን ዝርዝር መረጃ የምታገኙ መሆኑን አንገልፃለን።
ለበለጠ መረጃ፦
የጨረታውን ሙሉ ማስታወቂያ ለማግኘት የ telegram ወይም የ Facebook  ገፃችንን ይመልከቱ

ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ

ዲ.ዩ፦ ታህሳስ 11/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎት ትምህርትና ድጋፍ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀንን አከበረ። ቀኑ "አካታች የፈጠራ የስራና ሽግግራዊ መፍትሔ ለኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ሁለንተናዊ ተደራሽነት" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ነው የተከበረው።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ፍቃዱ ወ/ማርያም (ዶ/ር) የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት "ይህ በዓል ከሌሎች በዓላት በተለየ ሰብዓዊነት ጎልቶ የሚታይበት እና የሚታወስበት ልዩ በዓል በመሆኑ ከሌሎች ቀናት ለየት ያደርገዋል" ብለዋል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በባዮጋዝ ግንባታና ማዕድን አለኝታ ጥናት ዘርፍ ከደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል ማዕድን እና ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር በትብብር ለመስራት ስምምነት ተፈራረመ

ዲ.ዩ፦ ታህሳስ 07/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ በባዮጋዝ ግንባታና ማዕድን አለኝታ ጥናት ዘርፍ ከደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል ማዕድን እና ኢነርጂ ኤጀንሲ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውን የውል ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
የደቡብ ክልል ማዕድን እና ኢነርጂ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ አጸደ አይዛ 15 ሚሊየን ብር በሆነ ወጪ በባዮጋዝ ግንባታና በማዕድን አለኝታ ጥናት ዘርፍ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የውል ስምምነት ላይ መደረሱን ተናግረዋል።
ከዩኒቨርሲቲው ጋር በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ስለመሆኑም አስረድተዋል።

ለዲላ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ

ዲ.ዩ፦ ህዳር 29/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳሬክቶሬት ለዲላ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችና ባለሙያዎች ለሦስት ቀናት በህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ ሲሰጥ የቆየውን ስልጠና አጠናቋል።
አቶ ብሩህ ተስፋሁን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳሬክቶሬት የአጫጭር ስልጠናዎች አሰተባባሪ እንደገለጹት በህዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ዙርያ ክፍተት በሚታይባቸው ቦታዎች ላይ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ስልጠና ተሰጥቷል ብለዋል።

በቤተ- ሙከራ አደረጃጀትና አጠቃቀም ዙርያ ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፦ ሕዳር 29/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሳይንስ መምህራን በቤተ ሙከራ አደረጃጀትና አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል።
በዩኒቨርስቲው የማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተካልኝ ታደሰ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ፍኖተ ካርታ መሰረት በሀገር አቅፍ ደረጃ 55 በመቶ የተፈጥሮ ሳይንስ፣ እንዲሁም 45 በመቶ ደግሞ የማሕበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች እንዲሆን አቅጣጫ መቀመጡን አስታውሰዋል።

ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተከብረ

ዲ.ዩ፦ ህዳር 27/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን "ሙስናን መታገል በተግባር" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብሮ ውሏል። በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ18ኛ ጊዜ ተከብሯል።
በዓሉን በንግግር የከፈቱት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ችሮታው አየለ (ዶ/ር) "አሁን ላይ እንደ ሀገር ሙስናን ለመከላከል እየተደረገ ያለውን ከፍተኛ ጥረት መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በንቃት በመከታተል እና በመደገፍ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመታገል ግንባር ቀደም ተዋናይ ሊሆን ይገባል" ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

Pages