

ዲዩ ህዳር 02/2014 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነት) ተቋማችን ከአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የተመደበ በመሆኑ በተግባር ትምህርት እጃቸውን የፈቱ ሙሩቃንን ለማፍራት ቆርጦ እየሠራ መሆኑን የተናገሩት ዶ/ር ደረጀ ክፍሌ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምር/ቴክ/ሽግ/ምክ/ፕሬዝዳንት ተወካይ ከተቋማት ጋር የሚኖረን ትስስር በእጅጉ የጠበቀ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡
ከዚህ በፊት ስርዓተ ትምህርት ሲቀረፅ የኢንዲስትሪዎችን ፍላጎት ያገናዘበ እንዳልነበረ ተናግረው አሁን ላይ ከተለያዩ ፋብሪካዎችና ኢንዱስትሪዎች ፍላጎት እና የስራ እድል ከማስገኘት አኳያ ስርዓተ ትምህርት እየተቀረፀ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ዶ/ር ደረጀ አክለውም የደቡብ ሬድዮና ቴሌቭዝን ድርጅት ባለው ቴክኖሎጂ በመታገዝ እኛጋ ያለውን ዕውቀት በማስተሳሰር በክህሎቱ የተሻለ ዜጋ ለመፍጠር ይህን የመሰለ ስምምነት መፍጠራችን እገዛው የጎላ ነው ብለዋል፡፡
ዲ.ዩ ህዳር 3 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ስርጸት ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት ከጌዴኦ ዞን ከኮቸሬ፣ ከይርጋጨፌ፣ ከወናጎ እና ከዲላ ዙሪያ ወረዳዎች ለተውጣጡ እናቶች ማገዶ ቆጣቢ ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ ስልጠና ሰጠ። ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት በሚገኝበት አካባቢ ላይ የሀይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂ ላይ መስራት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ስርጸት ዳይሬክቶሬት ዶ/ር ሀብታሙ ተመስገን ስልጠናው የኖሮዌይ መንግስት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር ለመስራት በተስማማው መሰረት በትብብር የተዘጋጀ ስልጠና እንደሆነ ገልጸው በስልጠናው ከዚህ ቀደም ማገዶ ቆጣቢ ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ፣ በማኅበር ተደራጅተው በመስራት አምርተው የሚሸጡ፣ ባዮጋዝና ሶላር ኢነርጂን የሚጠቀሙ አዲስ እና ነባር ወደ 40 የሚደርሱ እናቶች መሳተፋቸውን ገልጸው በቀጣይ ሌሎች ወረዳዎችንም ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። ዶ/ር ሀብታሙ አክለውም የዲላ ዩኒቨርሲቲ የዚህ አይነት የትብብር ስራዎች ላይ በሩን ክፍት አድርጎ በመስራቱ እና ባለ
Public and International Relations Directorate
P.O.Box: 419
E-mail: pirdir@du.edu.et
Phone: +251461310001
: +251463312459
Dilla University
University of the Green Land!
The website Developed by DUICT Business App Dev't