ዲላ ዪኒቨርሲቲ በአንድ ስማርት ካርድና ባዮሜትሪክ ቴክኖሎጂን አካቶ የሚሰራ ማዕከላዊ የደህንነት አስተዳደር እና የተቀናጀ የመዳረሻ ቁጥጥር ስርዓት የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተደረገ::

ዲ.ዪ ህዳር 9/2014ዓ ም (ህዝብ ግንኙነት) ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የራሳቸውን ደህንነት ለማስጠበቅ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ተቋማችን ወደዚህ ስርዓት መግባት ወሳኝ ምዕራፍ ነው ያሉት ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት በግቢያችን የደህንነት ካሜራዎች በተለያዩ ቦታዎች ያሉ ቢሆንም central security management and intgrated access control system ለመተግበር ባለፉት ወራት ሰፊ ሰራ መሰራቱን ተናግረዋል::
ለስራው የሚያስፈልጉ መረጃዎችን በመስጠት ክፍሎች ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ አሳስበው ይህ የሚዘረጋው ስርዓት ተግባራዊ ሲሆን የተቋማችንን ደህንነትና ሰላማዊ የመማር ማስተማር አከባቢን ለመፍጠር ከማገዝ በላይ ማንኛውንም የደንበኞች መረጃ በቀላሉ ለማግኘት የሚያስችልና ውጤታማነትን የሚጨምር ነው ብለዋል::

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አደረገ።

ዲ.ዩ ህዳር 6 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለጀግናው መከላከያ ሠራዊት ያሰባሰበውን ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አስረከበ።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የተደረገውን ድጋፍ ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም የሀገርን ህልውና ለማስከበር ግዳጅ ላይ መስዋህትነትን እየከፈለ ለሚገኘው የሀገር መከላከያ ሠራዊት 3 ሚሊየን ብር በመለገስ አጋርነቱን ማሳየቱን ገልጸው ዛሬ ደግሞ ከዩኒቨርሲቲው ካፒታል በጀት 2 ሚሊዮን ድጋፍ እና ከሰራተኞች የወር ደሞዝ የተሰበሰበን በድምሩ 30 ሚሊዮን ብር እና በአይነት 200 ፍራሽ እንዲሁም 100 ተደራራቢ የብረት አልጋ ድጋፍ ማደረጉን ተናግረዋል ።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ዲዩ ህዳር 02/2014 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነት) ተቋማችን ከአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የተመደበ በመሆኑ በተግባር ትምህርት እጃቸውን የፈቱ ሙሩቃንን ለማፍራት ቆርጦ እየሠራ መሆኑን የተናገሩት ዶ/ር ደረጀ ክፍሌ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምር/ቴክ/ሽግ/ምክ/ፕሬዝዳንት ተወካይ ከተቋማት ጋር የሚኖረን ትስስር በእጅጉ የጠበቀ መሆን እንዳለበት ተናግረዋል፡፡

ከዚህ በፊት ስርዓተ ትምህርት ሲቀረፅ የኢንዲስትሪዎችን ፍላጎት ያገናዘበ እንዳልነበረ ተናግረው አሁን ላይ ከተለያዩ ፋብሪካዎችና ኢንዱስትሪዎች ፍላጎት እና የስራ እድል ከማስገኘት አኳያ ስርዓተ ትምህርት እየተቀረፀ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ዶ/ር ደረጀ አክለውም የደቡብ ሬድዮና ቴሌቭዝን ድርጅት ባለው ቴክኖሎጂ በመታገዝ እኛጋ ያለውን ዕውቀት በማስተሳሰር በክህሎቱ የተሻለ ዜጋ ለመፍጠር ይህን የመሰለ ስምምነት መፍጠራችን እገዛው የጎላ ነው ብለዋል፡፡

ከጌዴኦ ዞን ከተለያዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ እናቶች ማገዶ ቆጣቢ ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ የግንዛቤና የተግባር ስልጠና ተሰጠ።

ዲ.ዩ ህዳር 3 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ስርጸት ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት ከጌዴኦ ዞን ከኮቸሬ፣ ከይርጋጨፌ፣ ከወናጎ እና ከዲላ ዙሪያ ወረዳዎች ለተውጣጡ እናቶች ማገዶ ቆጣቢ ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገ ስልጠና ሰጠ። ከፍተኛ የሕዝብ ብዛት በሚገኝበት አካባቢ ላይ የሀይል ቆጣቢ ቴክኖሎጂ ላይ መስራት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ስርጸት ዳይሬክቶሬት ዶ/ር ሀብታሙ ተመስገን ስልጠናው የኖሮዌይ መንግስት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር ለመስራት በተስማማው መሰረት በትብብር የተዘጋጀ ስልጠና እንደሆነ ገልጸው በስልጠናው ከዚህ ቀደም ማገዶ ቆጣቢ ቴክኖሎጂን የሚጠቀሙ፣ በማኅበር ተደራጅተው በመስራት አምርተው የሚሸጡ፣ ባዮጋዝና ሶላር ኢነርጂን የሚጠቀሙ አዲስ እና ነባር ወደ 40 የሚደርሱ እናቶች መሳተፋቸውን ገልጸው በቀጣይ ሌሎች ወረዳዎችንም ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግረዋል። ዶ/ር ሀብታሙ አክለውም የዲላ ዩኒቨርሲቲ የዚህ አይነት የትብብር ስራዎች ላይ በሩን ክፍት አድርጎ በመስራቱ እና ባለ

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ካውንስል አባላት በጤና ሳይንሰ ኮሌጅና ሪፌራል ሆሰፒታል የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡

ዲ.ዪ ጥቅምት 26/2014 ዓ.ም. (ህ.ግ.) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሪፌራል ሆስፒታል በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ያሉበትን ተግዳሮቶች ለዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል አባላት በማቅረብ ጉዳዩን በጥልቀት ለመረዳት ጉብኝት መደረጉ ተገለፀ፡፡
ይህ የመስክ ጉብኝት ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ሪፌራል ሆስፒታል ያሉትን የአገልግሎት አሰጣጡን የለየና ለቀጣይ አቅጣጫ ያስቀመጠ እንደነበረ የገለፁልን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ አሁን ግንባታ ላይ ያለው ህንፃ በታቀደለት ጊዜ አለማለቁ አሁን ላይ እየታዩ ላሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ተግዳሮቶች አገዛ እንዳለው ገልፀው በህንፃው ዙሪያ ከኮነትራክተሩ ጋር በመነጋገር የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጥበት ሂደት እንደተመቻቸ ተናግረዋል፡፡

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሲያካሂድ የነበረዉ የመጀመሪያው ሀገር ዓቀፍ የSTEAM Research ኮንፍረንስ ተጠናቀቀ፡፡

ዲ.ዪ ጥቅምት 20/2014 ዓ/ም /ህ.ግ/ STEAM ማዕከል በሀገር ዓቀፍ ደረጃ ሆነ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረዉ በቅርብ ጊዜ ነዉ ያሉት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስ/ተማ/አገ/ምክ/ፕሬዚዳንት እና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ ያደጉ ሀገራት ተሞክሮ የሚያሳየን STEAM ላይ ጠንካራ ስራ መስራታቸዉ አሁን ላሉበት የእድገት ደረጃ እንዲደርሱ ከፍተኛ ሚና እነደነበረዉ ጠቅሰዉ እኛም ሀገራችንን ከድህነት እና ኋላ ቀርነት ለማላቀቅ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እዉቀትና ክህሎት የታነጸ ትዉልድ ማፍራት ለነገ የማይባል ስራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የመጀመሪያው ሀገር አቀፍ የSTEM ምርምር ኮንፈረንስ መካሄድ ጀመረ። ዲ.ዩ ጥቅምት 19 ቀን 2014ዓ.ም (ህ.ግ)

በኮንፈረንሱ የSTEM ሴንተር በሀገር ደረጃም ሆነ በዩኒቨርሲቲው በቅርብ ጊዜያት የተጀመረ ቢሆንም ወደፊት በሳይንሳዊ ጥናት ለሀገራችን ዕድገትና ብልጽግና ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
ኮንፈረንሱ "Challenges and prospects of STEAM Eduction in Ethiopia " በሚል መሪ ቃል ለሚቀጥሉት ሁለት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን በፕሮግራሙም የተለያዩ ጥናቶች ቀርበው ውይይት እንደሚካሄድባቸው ለማወቅ ተችሏል።
በዚህ በመጀመሪያው አገር አቀፍ የSTEM ምርምር ኮንፈረንስ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር እንግዶች ፣ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተመራማሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች አዲስ ከተሾሙት የጌዳኦ ዞን አስተባባሪ አባላት ጋር ትውውቅ እና በቀጣይ ሊኖር በሚገባው የስራ ግንኙነት ዙሪያ ውይይት አደረጉ::

ዲዪ ጥቅምት 15/2014 ዓ.ም. (ህዝብ ግንኙነት) በቀጣይ አብሮ ለመስራትና ለመተዋወቅ በመገናኝታችንና ህዝብን ለማገልገል በመመረጣችሁ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በራሴ ስም አንኳን ደስ አላችሁ ያሉት ዶክተር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት አንድ ተቋም ከተቋቋመበት አካባቢና ማህበረሰብ ተለይቶ ምንም ስራ መስራት እንደማይችል ገልፀው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለአከባቢው ማህበረሰብ በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ መቆየቱን ተናግረዋል::
አሁን ላይ ተቋሙ እየሰራ ያለውን ስራ ከታች ከህብረተሰብ አንስተን በማየት በቀጣይ ምን እንስራ÷ የተጀመሩትን ስራዎችን እንዴት እናስቀጥል÷ አዲስ ምን እንሰራ ብለን አብረን በመናበብ ለመስራት ይህ የውይይት መድረክ ሰፊ ፋይዳ አለው ብለዋል::

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል የአይን ህክምና ማዕከል ከኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በጌዴኦ ዞን ከ8 ወረዳዎች ለመጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ነፃ የአይን ህክምና በይርጋ ጨፌ ከተማ እየሰጠ ይገኛል፡፡

ዲ/ዩ ጥቅምት 8/2014ዓ.ም (ህ.ግ) ጤናዉ የተጠበቀ ዜጋ ለሀገር እድገትና ብልጽግና ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር እዮብ አያሌዉ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአይን ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል እና ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ከዛሬ ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 6 ቀናት በአይን ሞራ ምክንያት ማየት ለተሳናቸዉ ወገኖች የአይን ህክምና እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀው የአይን ሞራ የሚከሰተዉ በእድሜ ምክንያት በመሆኑ ህመም ያለበት ሰዉ በጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመምጣት መታከም ከቻለ የመዳን እድሉ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

Pages