

ዲዩ፤ ነሐሴ 9 ቀን 2011 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነት) የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት ከኮምፒውቲንግ እና እንፎርማቲክስ ትምህርት ቤት ጋር በመተባበር ሁለት ሺህ ለሚሆኑ ዜጎች መሠረታዊ የኮምፒውተር ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
የኮምፒውተር መሠረታዊ ዕውቀት(Computer Basics)፣ የበይነ መረብ አገልግሎቶች አጠቃቀም (The Internet, cloud services and world wide web)፣ የአገልግሎት ሰጪ መተግበሪያ ፕሮግራሞች አጠቃቀም(Productivity Programmes)፣ የዲጂታል አኗኗር (Digital lifestyles)፣ የግል መረጃ ደህንነት አጠባበቅ(Computer security and privacy) በዲጂታል መሠረተ ትምህርት (Digital Literacy) ስልጠና እየተዳሰሱ ያሉ ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው፡፡
በድጋሚ የወጣ የተማሪዎች ጥሪ ይመለከታል
በተለያየ ምክንያት የተማሪ ቅበላ ቀን ለውጥ አስፈልጓል፡፡
በመሆኑም የዲላ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተመራቂ ተማሪዎች፡-
በዲላ ዩኒቨርሲቲ በአረንጓዴ አሻራ ቀን ከ10 ሺህ በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተተከሉ
ዲዩ፤ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነት) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ የአረንጓዴ ቀንን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ የዕፅዋት ጥበቃና ኢኮ-ቱሪዝም ማዕከል ችግኝ ተከለዋል፡፡
ሐምሌ 22 ቀን 2011 ዓ.ም በታሪካዊው ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ ቀን የተቋሙ አመራሮች፣ ሠራተኞችና ተማሪዎች በነቂስ ወጥተው በችግኝ ተከላው ተሳትፈዋል፡፡
በተያዘው ዓመት ለአካባቢ ጥበቃ ልዩ ትኩረት በመስጠት በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረበው ጥሪ ሁሉንም ያነቃና አርአያነት ያለው ተግባር መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ተናግረዋል፡፡
የበረሀማነት መስፋፋትን ለመግታትና ብዝሀ ህይወትን ለመጠበቅ ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት መሠጠቱ አስፈላጊ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ፣ ማኅበረሰቡ ችግኝ ከመትከል ባለፈ የመንከባከብ ባህል ማዳበር ይኖርበታል በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
Public and International Relations Directorate
P.O.Box: 419
E-mail: pirdir@du.edu.et
Phone: +251461310001
: +251463312459
The website Developed by DUICT Business App Dev't