የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል በ2013 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ህ/ክ ጤና ቢሮ በኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ባስመዘገበው ውጤት የላቀ አፈጻፀም እውቅና ተሰጠው፡፡

ዲ.ዩ. ታህሳስ 02/2014 ዓ.ም. (ህ.ግ) የጤና ተቋማት ዋና ዓላማቸው በሽታን መከላከልና መቆጣጠር መሆኑን የተረዳው የዲላ ዩኒቨርስቲ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እየሰራ መሆኑን ገልፀው ሆስፒታሉ በላቀ ውጤት አፈፃፀም በክልል ጤና ቢሮ መሰጠቱ የተቋማችንን ሠራተኞች ብሎም ክፍሎችን ለላቀ ስራ የሚያነሳሳ መሆኑን የተናገሩት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንሰ ኮሌጅና ሪፌራል ሆስፒታል የህክምናና ተግባር ስልጠና ዋና ዳሬክተር ዶክተር ደረጀ ዳንኤል ይህን እውቅና ለሠራተኛው ለማሳወቅና ተነሳሽነቱን ለማጎልበት ሲነር ማናጂመንት አባላት ልዩ መድረክ ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል፡፡

በዲላ ዩኒቨርሲቲ በፐብሊክና ዲጅታል ዲፕሎማሲ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተካሄደ።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፐብሊክ ዲፕሎማሲ የሚኖራቸው ሚና የላቀ በመሆኑ ምሁራን ቴክኖሎጂዎችን ሁሉ በመጠቀም ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ማሸጋገር እንደሚጠበቅባቸው ተገለፀ።

..............

ዲ.ዩ ታህሳስ 1 ቀን 2014 ዓ.ም(ህ.ግ) የሳይንስ ሳምንት አካል በሆነው በፓናል ውይይት ላይ የተገኙ እንግዶችንና ተሳታፊዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስ/ተማ/አገ/ምክትል ፕሬዝዳንትና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ ይህ ወቅት መንግስት ለመንግስት ከሚያደርገው ዲፕሎማሲ ባሻገር ወደ ህዝብ ዲፕሎማሲ የተሻጋገርንበት ጊዜ በመሆኑ የህዝብ ዲፕሎማሲ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልጸው ይሁን እንጂ የህዝብ ዲፕሎማሲ ከሚሰጠው ጥቅም ባሻገር በጥንቃቄና በአግባቡ ካልተጠቀምንበት ለአፍራሽ ተልዕኮ ሊውል እንደሚችል መገንዘብ እንዳለብን ተናግረዋል።

በሥነ-ምግባር የታነጸ አመራር ከሙስና የፅዳች ኢትዮጲያ›› በሚል መሪ ቃል በአለም አቀፍ ደረጃ ለ18 ግዜ በሀገራችን ለ17 ግዜ የፀረ-ሙስና ቀን በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ::

ዲ-ዩ -ህዳር 30/2014ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነት) ሙስና የመንግስት እና የህዝብ ሀብት የግል ወይም የቡድን ፍላጎትን በህግ-ውጥ መንገድ ለግል ጥቅም ለሟሟላትና መልካም ስነ-ምግባር በሌላቸው ሰዎች የሚፈጸም፣ ተግባር፣ መሆኑን የተናገሩት ወ/ሮ መብራቴ ሽፈራው የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክተር የሙስና መከሰት ዋነኛ መንስኤው የመልካም ስነ-ምግባር እሴቶች መሽርሸር መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አክለውም ወ/ሮ ማብራቴ መልካም አስተዳደርና የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እንዲቀጭጭ የአገልግሎት አሰጣጡም ዜጎች በሚፈልጉት ደረጃ አንዳይሰጥ ያደርጋል ብለዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ 16ተኛውን የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በፓናል ወይይትና በተለያዩ መርሃ ግብሮች በታላቅ ድምቀት አከበረ፡፡

ዲ.ዩ. ህዳር 29/2014 ዓ.ም. (ህ.ግ.) ህገ-መንግሰቱ የፀደቀበት ቀን የብ/ብ/ህ ቀን ሆኖ ተሰይሞ በየአመቱ እንዲከበር የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሚያዝያ 21 ቀን 1998 ዓ.ም. መወሰኑን የተናገሩት ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት 'ወንድማማችነት ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነት' በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ የሚከበረው 16ተኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በዓል ልዩ የሚያደርገው ሀገር በህልውና ጦርነት ውስጥ ባለችበት ወቅት መሆኑና ኢትዮጵያን ለማፍረስ የራሳቸውን ፍላጎትና የምዕራባዊያንን ተልዕኮ ለማሳካት ከተሰለፉ ጎራዎች ጋር የሚደረግ ጦርነት ላይ ባለንበት ወቅት መሆኑ ነው ብለዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከጌዴኦ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ጋር በልማት ስራዎች ዙሪያ ስያካሂድ የነበረውን ውይይት አቅጣጫ በማስቀመጥ አጠናቀቀ፡፡

የዚህ ዓይነቱ የውይይት መድረክ ባለፉት ግዜያት ለማካሄድ ከፍተኛ ፍላጎት እንደነበረ የገለፁት ዶክተር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት  ከፍተኛ  የትምህርት ተቋማት ያሉበትን አከባቢ ማህበረሰብ በምርምር  በመደገፍ የማህበረሰብን ህይወት መቀየር ዋና መሪሃቸው መሆኑን ገልፀው እስካሁን በዞናችን ዘመናዊ የምርምር ውጤቶችን ከማዳረስ አኳያ እየተሰራ ያለው ስራ ውጤት እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ ከዞኑ አስተዳደር ጋር በማቀድ የማህበረሰብን የልማት ፍላጎት  ጥያቄ ለመመለሰ ከባለፈው ስራችን በበለጠ ለመሰራት ይህ መድረክ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለዞናችን ትልቁ ተቋማችን ነው ያሉን የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዮት  ደምሴ በበኩላቸው እሰካሁን የተሰሩት ስራዎች በርካታ ቢሆኑም አብሮ ተያይዞና አቅዶ የመስራት ረገድ ሰፊ ክፍተት መኖሩን ተናግረዋል፡፡

DU 3rd Science Week

"Science for Public and Digital Diplomacy"
08-10 December, 2021.
..............
We feel a great honor to invite you all to participate and take part in the 3rd Science Week to be celebrated at Dilla University with a series of science-related events for the general public from 08-10 December 2021.
It is a national program celebrated every November as part of “Building Science Culture”.

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከUNHCR ጋር በመተባበር በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ዙሪያ ያዘጋጀው ስልጠና በይርጋጨፌ ከተማ መካሄድ ጀመረ።

ዲ.ዩ ህዳር 23 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ህግና አስተዳደር ጥናቶች ኮሌጅ ከUNHCR ጋር በመተባበር በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መሠረታዊ መብት እና የሀገራት ግዴታ ዙሪያ በይርጋጨፌ ከተማ ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት ስልጠና ሰጠ።
በስልጠናው ላይ የተሳተፉ እንግዶችና ባለድርሻ አካላትን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ህግና አስተዳደር ጥናቶች ኮሌጅ በምርምር ዘርፍ ምክትል ዲን አቶ ተካልኝ ዱጌ ስልጠናው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት እንደሆነ ገልጸው በስልጠናውም የተፈናቃዮች መብቶች ምንድ ናቸው? የመንግስታትስ ግዴታስ ምንድነው? ተቋማትስ ለተጎጆዎች የሚያደርጉት ክትትልና ድጋፍ ምን መምሰል አለበት? የሚሉ ሃሳቦችን በስፋት ለማንሳትና ለችግሮቹም በጋራ መፍትሔ ለመስጠት እንደታሰበ ገልጸዋል።

Pages