የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሁለተኛ ቀን የመስክ ምልከታ ዛሬም ተካሂዷል

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 26/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ከትላትን ጀምሮ የመስክ ምልከታ በዲላ ዩኒቨርሲቲ እያካሄዱ እንደሆነ መዘገባችን አይዘነጋም።
በቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሬ ሌንጮ (ዶ/ር) የተመራው ቅኝት አድራጊ ቡድን ዛሬ ከሰአት በፊት በዲላ ዩኒቨርሲቲ እየተከናወኑ ያሉ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችን ተመልክቷል።

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በዛሬ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከሰአት በኋላ ቆይታቸው ልዩ ልዩ የመስክ ምልከታዎችን አካሂደዋል

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ምልከታ እያካሄዱ እንደሆነ ዛሬ ጧት መዘገባችን የሚታወስ ነው።

የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ውይይት ተካሄደ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 24/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል ጉባዔ በዩኒቨርሲቲው የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ዛሬ ውይይት አካሂዷል።
በውይይት መድረኩ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸሞች ለመድረኩ ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።

የአባያ-ጫሞ ንዑስ ተፋሰስ ጥናት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ''ዎርክሾፕ'' ተካሄደ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 19/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ተፋሰስ አስተዳደር ፅ/ቤት በጋራ ትብብር የሚያከናውኑትን የውሃ ጥናት "ABAYA - CHAMO SUB-BASIN WATER ALLOCATION PLANNING" የማስጀመሪያ "ዎርክሾፕ" በዛሬው እለት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ "ኢንፎ ማይንድ ሶሉሽንስ" ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 11/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ "ኢንፎ ማይንድ ሶሉሽንስ" ከተባለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ጋር በተመራቂ ተማሪዎች ዙሪያ አብሮ ለመስራት የሚያስችል የስምምነት ሰነድ መፈራረሙ ተገልጿል።
ማቴዎስ ሀብቴ (ዶ/ር )፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ፤ የተጠቀሰው ድርጅት በተመራቂ ተማሪዎች ዙሪያ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የውል ስምምነት ላይ መድረሱን ነው የገለፁት።

Pages