ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የሳይንስ ሳምንት መርሃግብር ተጠናቀቀ

ዲ.ዩ፦ ህዳር 16/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ስርፀት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት "ሳይንስ ለምግብ ዋስትና እና ሉአላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ ሲከናወን የቆየው አራተኛው የሳይንስ ሳምንት ፍጻሜውን አግኝቷል።
በመርሃግብሩ ወቅት ንግግር ያደረጉት ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት በሀገራችን አመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞችንና ለም መሬት ይዘን የምግብ ዋስትናችንን ባለማረጋገጣችን ምክንያት በተጽእኖ ውስጥ እንድንወድቅ ሆነናል ብለዋል።
አያይዘውም ሀገሪቷ ያስተማረቻቸው ምሁራን በአገራችን ያለውን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የተሻለ ስራ ለመስራት ጥናትና ምርምር ማድረግ እንዲሁም ጥናቱን ወደ ተግባር መለወጥ ይጠበቅብናል ሲሉ አሳስበዋል።

Dilla University receives educational simulator and machine donations

DU: Nov. 23, 2022 (P.I.R) Dilla University's College of Medical and Health Sciences received educational simulators and machine donations from Health Professional Education Partnership Initiative for its skill improvement center for medical students.
The surgical specialist and Health Professional Education Initiative coordinator at Dilla Center, Dr. Tesfaw Bekele, received the donations and submitted them to the skill hub coordinator. The donation includes dolls and machines with simulation equipment.

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርደ በዩኒቨርሲቲው ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ ከተቋሙ ከፍተኛ አመራር ጋር ተወያየ

ዜና ትንታኔ ዲ.ዩ፡- ህዳር 03/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ በዩኒቨርሲቲው የ2014 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2015 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ዝርዝር ውይይት አካሄደ፡፡ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዋ እና የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እና የስራ አመራር ቦርዱ አባላት በውይይቱ ተገኝተዋል፡፡ በእለቱ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በአራቱ የምክትል ፕሬዝዳንት ፅ/ቤቶች፣ በህክማና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል እንዲሁም የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት እና በስሩ ያሉ ባለ ብዙ ዘርፍ ፅ/ቤቶች ባለፈው አመት ያከናወኗቸው ተግባራት አፈፃፀም ሪፖርቶች ቀርበዋል፡፡ በዝርዝር ሪፖርቶቹ በአመቱ የታቀዱ፣ የተከናወኑ ተግባራት እንዲሁም በአፈፃፀም የተገኙ እምርታዎች እና ጉድለቶች ከተወሰዱ መፍትሄዎች ጋር በዝርዝር ተዳስሰዋል፡፡

የ‹ሲ.ቲ ስካን› ማሽን ስራ መጀመሩ ተገለጸ

ዲ.ዩ፡- ጥቅምት 15/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል ከ45 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገዛው የ‹ሲ.ቲ ስካን› ማሽን ስራ መጀመሩ ተገለጸ፡፡ ሆስፒታሉ የህክምና ስራዎቹን ለማሳለጥ እና ተደራሽነት ለማስፋት ከሚጠቀመው ዘመናዊ የሕክምና መሳሪያዎች አንዱ መሆኑን ነዉ የተገለጸው።
በዩኒቨርሲቲው የሕክምና እና ሳይንስ ኮሌጅ እና ጠቅላላ ሆስፒታል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምጽዋ ሩፎ ሆስፒታሉ ከጌዴኦ ዞን፣ ኦሮሚያ እና ሲዳማ አጎራባች ክልሎች ለሚመጡ ከፍተኛ ቁጥር ላለው ሕብረተሰብ የሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል፡፡

For all Regular Students of Dilla University

1) If you are a first-year (freshman) student and will start your second semester, you will report on Tikimt (ጥቅምት) 28 and 29, 2015 e.c.
2) Third year and above (3rd, 4th, and 5th) year students, we would like to inform you that the dates you will have to come and register at the university are Hidar (ህዳር) 05 and 06, 2015 e.c.
3) Students from the Health and Medical Sciences College will report according to the previous call.

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የመጀመሪያ ዙር በሰላም መጠናቀቁ ተገለፀ

ዲ.ዩ፦ ጥቅምት 02/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስቱም ግቢዎች ለሶስት ተከታታይ ቀናት የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም ተጠናቋል።
በዋናው፣ ኦዳያአ እና ሐሴዴላ ግቢዎች ከተፈተኑት ከ16 ሽህ 800 በላይ ተማሪዎች መካከል ከቅርብ ርቀት የመጡት ተማሪዎች ወደየ አካባቢያቸው እየተሸኙ ሲሆን ሌሎች በተያዘላቸው የጉዞ መርሃግብር መሰረት የሚሸኙ ይሆናል።
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሰጥ ከተወሰነ ጀምሮ በተቋሙ መዋቅር፣ የፀጥታ አካላት፣ ትምህርት ሚኒስቴር፣ እንዲሁም የአካባቢው አስተዳደር እና የሚመለከተው ባለ ድርሻ አካላት ሁለ ተሳትፎ ያደረጉበት ዝግጅት እንደ ነበር የገለፁት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንትና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ ዶ/ር ፍቃዱ ወ/ማርያም ናቸው።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ ስር የኪነ-ህንፃ ምህንድስና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎችን አስመረቀ::

ዲ.ዩ መጋቢት 3/2014 ዓ.ም. (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ የኪነ ህንፃና የግንባታ ምህንድስና ትምህርት ቤት የኪነ-ህንፃ ምህንድስና (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡
የቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ መምህራንና ኃላፊዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች እንግዶችና ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በታደሙበት ነው ምረቃቱ የተካሄደው።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረጉ የተፈጥሮ ሀብት እና ግብርና ስራዎችን በተቀናጀ ሁኔታ እያከናወነ መሆኑን ገለፀ::

የዲላ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ መሰረት የተግባር ተኮር (Applied) ዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ የተካተተ ነው። በዚህም መሰረት ዩኒቨርስቲው በትኩረት ከሚሰራባቸው መስኮች መካከል የግብርና እና ተፈጥሮ ሃብት አያያዝ ዋነኛው ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ዩኒቨርሲቲው ለአካባባው ማህበረሰብ ተደራሽ እንዲሆን የዕውቀት፣ የቴክኖሎጂና የክህሎት እገዛ ለማድረግ ከአካባባው ማህበረሰብ ፍላጐት ጋር የሚጣጣም ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ዩኒቨርሲቲው የሚገኝበት አካባባ ጥምር ደን ግብርና እንዲሁም ከፊል አርብቶ አደር ሥልተ ምርት የሚከናወንበት በመሆኑ የልማት እገዛ ተግባራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ስራዎችን ያከናውናል፡፡ ከዚህ አኳያ በጥምር የደን ግብርና ሥራ ዙሪያ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ የአካባቢ ዝርያዎች የመጠበቅና የዝርያ ማሻሻል ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴት መምህራንን የምርምር ስራዎች ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ ያለመ ምክክር ተካሄደ::

ዲ.ዩ. የካቲት 25/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴት መምህራንን የምርምር ስራዎች ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ ያለመ ምክክር ተካሄደ። የምክክር መድረኩ በዩኒቨርሲቲው የስርአተ-ፆታ ዳይሬክቶሬት ከምርምር እና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ጋር በትብብር የተዘጋጀ ነው።
ያለ ሴቶች ተሳትፎ የሚያድግ ሀገርም ሆነ ህብረተሰብ የለም ያሉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴ/ህ/ወ/ጉ ዳይሬክተር ወ/ሮ አለሚቱ ብርሃኑ ጽ/ቤታቸው ዩኒቨርሲቲው በሚያዘጋጀው ስትራቴጂክ እና ዓመታዊ እቅዶች ላይ የሴት መምህራን እና ተመራማሪዎች እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ግቦች የበለጠ ትኩረት እንዲያገኙ እንሰራለን ብለዋል።
ኃላፊዋ አክለውም አመልካች ግቦችን በማስቀመጥ ሊለኩ የሚችሉና በውጤታማነት የሚተገበሩ እቅዶች እንዲዘጋጁና እንዲተገበሩ የሚያስችሉ ስራዎች ላይ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

Pages