ለቅድመ ምረቃ እጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዛሬ መሰጠት ጀምሯል

ዲ.ዩ፦ ሐምሌ 03/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለቅድመ ምረቃ እጩ ተመራቂዎች በትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀውን አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና በዛሬው እለት መስጠት ጀምሯል።
ታምራት በየነ (ዶ/ር፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት፤ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በተማሩበት የትምህርት መስክ ከፍተኛ ግንዛቤ ያላቸውንና በራሳቸው የሚተማመኑ ተመራቂዎችን ለማፍራት ዘርፈ ብዙ ስራዎች በመሰራት ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ ከነዚህ መካከል አንዱ የመውጫ ፈተና መስጠት እንደሆነ ገልፀዋል።

ለተከታታይ አምስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ተማሪዎች ፈተና ተጠናቀቀ

ዲ.ዩ፦ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በአገር አቀፍ ደረጃ የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩ ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረው ፈተና ዛሬ ተጠናቋል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲም በዚሁ ፕሮግራም ተቀብሎ የማጠናከሪያ ትምህርት ሲሰጣቸው የቆዩትን ተማሪዎች ፈትኗል፤ የፈተናውን ደህንነትና ሚስጥራዊነት በማስጠበቅ ረገድ ትኩረት ሰጥቶ ከፀጥታ ግብረ ኃይሉ ጋር በመቀናጀት ለ2400 በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ እና ከ1600 በላይ የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ተማሪዎች ፈተናውን ሰጥቷል።

የባዮጋዝ ልማት ስሥራዎችን የመገምገምና የመከታተል ስራ ተካሄደ

ዲ.ዩ፦ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም( ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጀንስ ጋር በመተባበር በጌዴኦ ዞን በወናጎና በይርጋጨፌ ወረዳዎች እየተገበረ ያለውን የባዮጋዝ ልማት ስራዎች ክትትልና ግምገማ ተደረገ።
ችሮታው አየለ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት፤ የባዮጋዝ ኘሮጀክቱ ከደቡብ ክልል ማዕድንና ኢነርጂ ኤጄንስ ጋር በመተባበር እንደሚሰራ ገልጸው፤ ማዕዲንና ኢነርጂ ዘጠኝ ሚሊየን፣ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሁለት ሚልየን እንደሚሸፍኑ አብራርተዋል። ቀሪው ደግሞ ከተጠቃሚው ማህበረሰብ በግብዓት መልክ የሚሰበሰብ ሆኖ በአጠቃላይ 13 ሚሊዮን ብር ተመድቦለት የተጀመረ ፕሮጀክት ነው ተብሏል።

የቅጥር እና የስራ ዝግጁነት ክህሎት የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፦ ሰኔ 03/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ"ደረጃ ዶት ኮም" ጋር በመተባበር ከተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ለተመረጡ መምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጥቷል። እነዚህ መምህራን በቀጣይ ለሚመረቁ ተማሪዎች የቅጥር እና የስራ ዝግጁነት ክህሎት የሚያሰለጥኑ መሆኑ ታውቋል።
ደሳለኝ አዳሙ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የፊዚክስ ትምህርት ክፍል መምህርና የስነ ውጤት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር፤ የዩኒቨርሲቲያችን ተማሪዎች ተመርቀው ከመውጣታቸው በፊት ስለ ስራ አፈላለግ ራሳቸውን ቀድመው ከስራ ጋር ሊያዛምዱ የሚችሉባቸውን የተለያዩ ስልጠናዎችን ለመስጠት በዩኒቨርሲቲያችን መምህራኖችን ቀድሞ በማሰልጠን፤ የሰለጠኑ መምህራን ደግሞ በቀጣይ ተመራቂ ተማሪዎቻችንን እንዲያሰለጥኑ በማሰብ የተሰጠ የአሰልጣኞች ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል።

DU trains on "Turnitin" software, which permits checking similarities between research works

DU: June 6, 2023 (P.I.R): Skill development training is given on the "Turnitin" software, which aims to check the similarity of research papers. The training is given to postgraduate lecturers, journal board members, thematic leaders, and research council members (ad hoc).
The training was organized in cooperation with the Dilla University Research and Technology Transfer Vice President's office, the Directorate of Research and Dissemination, and the Postgraduate School.

የምርምር ሥራዎችን ተመሳስሎት ለመፈተሽ በሚያስችል የ"Turnitin " ሶፍትዌር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፡- ግንቦት 29/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፡- የምርምር ስራዎችን ተመሳስሎት ለመፈተሽ (Similarity Checker) በሚረዳ "Turnitin" በተሰኘ ሶፍትዌር ላይ የክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናው የተሰጠው ለድህረ-ምረቃ አስተማሪዎች፣ ለጆርናል ቦርድ አባላት፣ ለምርምር ጭብጥ መሪዎች እና ለምርምር ካውንስል አባላት ነው።
ስልጠናውን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምር/ቴክ/ሽግ/ም/ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ከምርምርና ስርፀት ዳይሬክቶሬት እንዲሁም የድህረ-ምረቃ ትምህርት ቤት በጋራ አዘጋጅተውታል።

Pages