የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የመጀመሪያ ዙር በሰላም መጠናቀቁ ተገለፀ

ዲ.ዩ፦ ጥቅምት 02/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስቱም ግቢዎች ለሶስት ተከታታይ ቀናት የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም ተጠናቋል።
በዋናው፣ ኦዳያአ እና ሐሴዴላ ግቢዎች ከተፈተኑት ከ16 ሽህ 800 በላይ ተማሪዎች መካከል ከቅርብ ርቀት የመጡት ተማሪዎች ወደየ አካባቢያቸው እየተሸኙ ሲሆን ሌሎች በተያዘላቸው የጉዞ መርሃግብር መሰረት የሚሸኙ ይሆናል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ ስር የኪነ-ህንፃ ምህንድስና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎችን አስመረቀ::

ዲ.ዩ መጋቢት 3/2014 ዓ.ም. (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ የኪነ ህንፃና የግንባታ ምህንድስና ትምህርት ቤት የኪነ-ህንፃ ምህንድስና (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡
የቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ መምህራንና ኃላፊዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች እንግዶችና ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በታደሙበት ነው ምረቃቱ የተካሄደው።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረጉ የተፈጥሮ ሀብት እና ግብርና ስራዎችን በተቀናጀ ሁኔታ እያከናወነ መሆኑን ገለፀ::

የዲላ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ መሰረት የተግባር ተኮር (Applied) ዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ የተካተተ ነው። በዚህም መሰረት ዩኒቨርስቲው በትኩረት ከሚሰራባቸው መስኮች መካከል የግብርና እና ተፈጥሮ ሃብት አያያዝ ዋነኛው ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ዩኒቨርሲቲው ለአካባባው ማህበረሰብ ተደራሽ እንዲሆን የዕውቀት፣ የቴክኖሎጂና የክህሎት እገዛ ለማድረግ ከአካባባው ማህበረሰብ ፍላጐት ጋር የሚጣጣም ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ዩኒቨርሲቲው የሚገኝበት አካባባ ጥምር ደን ግብርና እንዲሁም ከፊል አርብቶ አደር ሥልተ ምርት የሚከናወንበት በመሆኑ የልማት እገዛ ተግባራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ስራዎችን ያከናውናል፡፡ ከዚህ አኳያ በጥምር የደን ግብርና ሥራ ዙሪያ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ የአካባቢ ዝርያዎች የመጠበቅና የዝርያ ማሻሻል ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴት መምህራንን የምርምር ስራዎች ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ ያለመ ምክክር ተካሄደ::

ዲ.ዩ. የካቲት 25/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴት መምህራንን የምርምር ስራዎች ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ ያለመ ምክክር ተካሄደ። የምክክር መድረኩ በዩኒቨርሲቲው የስርአተ-ፆታ ዳይሬክቶሬት ከምርምር እና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ጋር በትብብር የተዘጋጀ ነው።
ያለ ሴቶች ተሳትፎ የሚያድግ ሀገርም ሆነ ህብረተሰብ የለም ያሉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴ/ህ/ወ/ጉ ዳይሬክተር ወ/ሮ አለሚቱ ብርሃኑ ጽ/ቤታቸው ዩኒቨርሲቲው በሚያዘጋጀው ስትራቴጂክ እና ዓመታዊ እቅዶች ላይ የሴት መምህራን እና ተመራማሪዎች እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ግቦች የበለጠ ትኩረት እንዲያገኙ እንሰራለን ብለዋል።
ኃላፊዋ አክለውም አመልካች ግቦችን በማስቀመጥ ሊለኩ የሚችሉና በውጤታማነት የሚተገበሩ እቅዶች እንዲዘጋጁና እንዲተገበሩ የሚያስችሉ ስራዎች ላይ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

በዲላ ዩኒቨርሲቲ በሥነ ምግባር ምንነት ፅንሰ ሃሳብና አስፈላጊነት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አዲስ ለተቀጠሩ መምህራን ተሰጠ::

ዲ.ዩ. የካቲት 24/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ምግባር ምንነት ፅንሰ ሀሳብ እና አስፈላጊነት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አዲስ ለተቀጠሩ መምህራን ሰጠ።  የዩኒቨርሲቲው የሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ከሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ጋር በመሆን ነው ስልጠናውን ያዘጋጁት።
መምህራን ወደ ሥራ ከመሰማራታቸው በፊት ስለ ተቋሙ አጠቃላይ ገፅታና ባህሪ እንዲሁም የመንግስት ሠራተኞች የሚመሩበትና የሚተዳደሩበትን ህግና ደንቦች ማሳወቅ አስፈላጊ በመሆኑ ነው ስልጠናው የተሰጠው ተብሏል።
አዲስ ገቢ መምህራኑ በቀጣይ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲሰሩ እና የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችላቸውን ስልጠና አግኝተዋል ብለዋል፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ፀጋ፡፡

126ኛ አመት የአድዋ ድል መታሰቢያ በአል ምክንያት በማድረግ ዶክተር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ያስተላለፉት መልዕክት

"ለመላው ኢትዮጵያዊያን፣ የኢትዮጵያ ወዳጆች፣ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች፦ እንኳን ለ126ኛ አመት የአድዋ ድል መታሰቢያ በአል በሰላም አደረሳችሁ።
ይህንን በአል ስናከብር ጥንት አባቶቻችን የውጪ ጠላት በመጣ ጊዜ የውስጥ ልዩነታቸውን ወደ ጎን በመተው የውጪ ወራሪን በአንድነት ተፋልመው ድል እንዳደረጉ ሁሉ፣ ዛሬም ሐገራችን ወጥረው የያዟት ዘርፈ ብዙ የውጪ እና የውስጥ ጠላቶች አሏት። ዛሬም ሐገራችን አንድነቷን የሚፈታተን ፍልሚያ አለባት። ዛሬም ሐገራችን በአንድነት ቁመን እንድንታገልላት፣ ክብሯን፣ ነፃነቷን እንድናስጠብቅላት፣ በልዩነታችን እየተገፋፋን ለጠላት እድል ከማስፋት ይልቅ በአንድነታችን እየተደጋገፍን በህብረት ቁመን ዘርፈ ብዙ ድል እንድናጎናፅፋት ትሻለች።

Pages