በታዳሽ ኃይል ልማትና የአቅም ግንባታ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተካሄደ

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት በይርጋጨፌ ከተማ ከጌዴኦ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ እማወራዎች በተደራሽ ኃይል ልማትና የአቅም ግንባታ ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል።
መድረኩ በታዳሽ ኃይል ልማትና የአቅም ግንባታ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር የተካሄደበት ሲሆን፤ በመድረኩ ለተሳተፉ እማወራዎችም በማገዶ ቆጣቢ ምድጃ አሰራርና አጠቃቀም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቶበታል።
የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ጌቱ ታምሩ፣ የይርጋጨፌ ወረዳ አስተዳዳሪ፤ በዓለም ላይ የሚታወቀውን ባለ ልዩ ጣዕም ቡና ወደምትሰጠው ይርጋጨፌ ወረዳ እንኳን በሰላም መጣችሁ በማለት እንግዶችን ተቀብለዋል።

የ12ኛ ክፍል ፈተና አስፈፃሚዎች በጌዴኦ ዞን የሚገኙ የትክል ድንጋይ መካነ-ቅርሶችን ጎበኙ

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 23/2015 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ለ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተመድበው የፈተና ሂደቱን ሲያስፈጽሙ የቆዩ መምህራን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቱሪስት መስህብ የሆኑትን የጨልባ ቱቲቲ ታሪካዊ ትክል ድንጋዮች ጎብኝተዋል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከጌዴኦ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ፈተና መጠናቀቁን ተከትሎ የጉብኝት መርሃግብር አዘጋጅተዋል።

የመጀመሪያ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መጠናቀቁን ተከትሎ ተማሪዎች ወደ አካባቢዎቻቸው እየተሸኙ ነው

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፡- የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መጠናቀቁን ተከትሎ ተማሪዎች ወደ አካባቢዎቻቸው እየተሸኙ ነው።
በአገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ እየተሰጠ የሚገኘው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስቱም ጊቢዎች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ፤ የመጀመሪያ ዙር ማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ትላንት በነበረ የከሰአት የፈተና መርሃግብር መጠናቀቁ ይታወሳል።

በመጀመሪያ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች ገለጻ ተሰጠ

ዲ.ዩ፡- ሐምሌ 18/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ):- የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሰጠት ከተጀመረ ሁለተኛ ዙር በሆነው የዘንድሮው ፈተና መርሃግብር በዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የመጀመሪያ ዙር ማለትም የማሕበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ስለ ፈተና አሰጣጥና በግቢ ውስጥ ስለሚኖራቸው ቆይታ ገለጻ (Orientation) ተደርጎላቸዋል፡፡
ችሮታው አየለ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በገላጻው ወቅት እንደተናገሩት፤ ከደ/ብ/ብ/ሕ/ ክልል ጌዴኦ ዞን፣ ከአጎራባች የሲዳማ ክልል አካባቢዎች፣ እንዲሁም ከሶማሌ ክልል ተመድበው ወደ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለመጡ ተፈታኝ ተማሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

የመጀመሪያ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ከትላንት ጀምሮ ወደ ዲላ ዩኒቨርሲቲ እየገቡ ነው።

ዲ.ዩ፡- ሐምሌ 17/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮ የትምህርት ዘመን በመጀመሪያው ዙር (ማህበራዊ ሳይንስ) የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ከትላንት ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲ እየገቡ ነው። ዲላ ዩኒቨርሲቲ በሁለቱም ዙር 17 ሽህ አካባቢ ተማሪዎች ተቀብሎ ይፈትናል።
የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎቹ ዛሬ ተጠቃለው የሚገቡ ሲሆን የቅድመ ፈተና ገለፃ (Orientation) ነገ ይሰጣል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፍ የተገበራቸውን ፕሮጀክቶች መርቆ አስረከበ

ዲ.ዩ፦ ሐምሌ 15/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ በማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት በኩል የተገበራቸውን ፕሮጀክቶች የምረቅና ርክክብ መርሃግብር አካሄደ።
አቶ ተካልኝ ታደሰ፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክተር፤ በዛሬው ዕለት በተካሄደው የርክክብ ምረቃ ሥነ-ስርዓት እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን (UNHCR ) እና ከአካባቢዎቹ አስተዳደር ጋር በመተባበር የገነባቸውን ነፃ የሕግ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጋቸውን ገልፀዋል።

የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኞችን ተቀብሎ ለመፈተን ዝግጅቶች መጠናቀቃቸው ተገለፀ

ዲ.ዩ፦ ሐምሌ 15/2015 ዓ.ም(ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሁለተኛ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኞችን ተቀብሎ ለማስፈተን ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል።
ችሮታው አየለ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት፤ እንደ ሀገር በተያዘው አቅጣጫ መሰረት ፈተናው በዩኒቨርሲቲዎች መሰጠቱ ኩረጃና ማጭበርበርን ለማስቀረት ወሳኝ ነው ብለዋል።
ተማሪዎች ፈተናቸውን በራሳቸው ጥረትና አቅም እንዲሰሩ ለማድረግና የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት አንድ አካል መሆኑንም ነው ፕሬዝዳንቱ ያስገነዘቡት። አያይዘውም፤ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተናገድና የፈተና ሂደቱን በስኬት ለማጠናቀቅ ሙሉ ዝግጅት ማድረጉን ገልጸዋል።

Pages