በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶአደሮች የቀርቀሃ ችግኝ ስርጭት ተካሄደ

ዲ.ዩ፦ ሚያዝያ 12/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት በጌዴኦ ዞን ቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የቀረቀሃ ችግኝ ስርጭት አካሂዷል።
ደረጄ ክፍሌ (ዶ/ር) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ኘሬዝዳንት፤ ከአምስት አመታት በፊት ጀጎ ላይ የነበረው የቀርቀሃ ደን የመጥፋት አደጋ አጋጥሞት እንደነበር አስታውሰው፤ ደኑን መልሶ ለማልማት የአምስት አመት ኘሮጀክት በመንደፍ ወደ ስራ በመገባቱን አሁን ላይ ወደ 4.5 ሄክታር የቀርከሃ ደን መልሶ ማልማት ተችሏል ብለዋል።

የአኘል ምርት በቡሌ ወረዳ የሚገኙ አርሶአደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው

 
ዲ.ዩ: መጋቢት 26/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት የአኘል ምርት በቡሌ ወረዳ የሚገኙ አርሶአደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
አቶ ተካልኝ ታደሰ የዳሬክቶሬት ፅ/ቤቱ ዳይሬክተር እንደገለጹት፤ በዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት ስር ተደራሽ ከሚደረጉ ኘሮጀክቶች መካከል የመካከለኛውና የደጋማ አከባቢዎችን የሚሸፍነው የድንች፣ ቀርቀሃ፣ እንሰትና አኘል ልማት ናቸው ብለዋል።
አሁን ላይ በትኩረት እየተሰራ ያለው የአኘል ምርት ላይ መሆኑን ገልጸው፣ የጌዴኦ ዞንና አከባቢው በብዛት የሚታወቅበት የቡና ምርት በይበልጥ በወይናደጋው እና ቆላ አካባቢ በመሆኑ የደጋውን አካባቢ ደግሞ በአኘል ምርት ታዋቂ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር በሰጠው መሬት ላይ በምርምር ያለማውን የእንሰት ችግኝ ለአርሶ አደሮች አሰራጨ

ዲ.ዩ፦ መጋቢት 22/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት በሳይንሳዊ መንገድ የበለጸጉ የእንሰት ችግኞችን በጌዴኦ ዞን ሁለት ወረዳዎች ውስጥ ለተመረጡ አርሶአደሮች አሰራጭቷል።
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ኘሬዝዳንት ደረጄ ክፍሌ (ዶ/ር)፤ በምርምር ለምቶ ለአርሶአደሮች የተሰራጨው የእንሰት ችግኝ በዩኒቨርሲቲው ተደራሽ ከሚደረጉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው ብለዋል። ዲላ ዩኒቨርስቲ የአከባቢውን ማህበረሰብ ኑሮ በማሻሻል ገቢውን ለማሳደግ ተመሳሳይ በርካታ ስራዎችን መስራቱንም ገልፀዋል።

Dilla University Strengthens Women's Participation in Research and Leadership

D.U: March 25, 2023 (P.I.R.): Dilla University, Research and Dissemination Directorate, in collaboration with the NORHED ll ReRED project, held a discussion aimed at increasing the integrated research and leadership capacity of women academicians.
At the public lecture, Professor Alison Brown from Cardiff University, England, presented a public lecture titled "Enhancing Women's Participation in Collaborative Research and Academic Leadership."

የሴቶችን የምርምርና አመራርነት ተሳትፎ ማጎልበት እንደሚገባ ተገለጸ

ዲ.ዩ፦ መጋቢት 16/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ከNORHED ll ReRED ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የሴቶችን የተቀናጀ የምርምርና አመራርነት አቅም ለማሳደግ ያለመ የውይይት መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ ከእንግሊዝ ሀገር ካርዲፍ ዩኒቨርሲቲ (Cardiff University) የመጡት ፕሮፌሰር አሊሰን ብራውን የሴቶችን የተቀናጀ የምርምርና አመራርነት ተሳትፎ ማጎልበት (Enhancing Women's participation in collaborative Research and Academic leadership) በሚል ርዕሰ ገለጻ አቅርበዋል።
ፕሮፌሰሯ በገለጻቸው እስከዛሬ በህይወት እና ሙያ መስካቸው ያካበቷቸውን ልምዶችና እውቀቶች ለመድረኩ ተሳታፊዎች አካፍለዋል።

የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ስራ አስኪያጅ ደራሲ የዝና ወርቁ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ከመምህራን እና ተማሪዎች ጋር ተወያዩ

ዲ.ዩ፦ መጋቢት 14/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ስራ አስኪያጅ ደራሲ የዝና ወርቁ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ከመምህራን እና ተማሪዎች ጋር ትምህርታዊ ውይይት አካሄዱ። ደራሲ የዝና ወርቁ በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ዘመናዊ አጭር ልቦለድ ደራሲ ሲሆኑ የህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ከፍተኛ ባለሙያ እና በልዩ ልዩ ጋዜጦች ዋና አዘጋጅ ሆነውም ሰርተዋል።
በዩኒቨርሲቲው ማኅበራዊ ሳይንስ እና ሥነ -ሰብዕ ኮሌጅ የአማርኛ ቋንቋና ሥነ- ጽሑፍ ትምህርት ክፍል ያሰናዳው ይህ ትምህርታዊ ውይይት ዛሬ በ"LH4" ሴሚናር አዳራሽ የተካሄደ ሲሆን መምህራን፣ ተማሪዎች እና የሥነ-ጽሁፍ አድናቂዎች ታድመውበታል።

"በዩኒቨርሲቲያችን የመውጫ ፈተናን በአግባቡ ለመስጠት ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ነው"

ማቴዎስ ሀብቴ (ዶ/ር)
የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ
ዲ.ዩ፦ መጋቢት 8/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ከያዝነው 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስትና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ ለማድረግ የታቀደውን የመውጫ ፈተና (Exit exam) ዲላ ዩኒቨርስቲ ለተመራቂ ተማሪዎቹ በ"ኦንላይን" ለመስጠት የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
ማቴዎስ ሀብቴ (ዶ/ር) የዲላ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ፤ መንግስት ከትምህርት ጥራት ጋር ተያይዞ እንደ ሀገር ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመቀነስ በማሰብ በመጪው ሐምሌ ወር በመንግስት እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ የያዘለትን የመውጫ ፈተና ዩኒቨርሲቲው በብቃት ለመስጠት ሰፊ የዝግጅት ስራዎች እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።

ዓለማቀፉ የሴቶች ቀን "ማርች 8"ን ተንተርሶ በ"እናት" መፅሐፍ ላይ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ

ዲ.ዩ መጋቢት 8/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርስቲ "ማርች 8" የሴቶች ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ112ኛ ጊዜ “ፈጠራና ቴክኖሎጂ ለጾታ እኩልነት” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል።
በእለቱም ጭብጡን ሴትነትን ከቤተሰብ ህይወት እስከ ማህበረሰባዊ ሁለንተናዊ ጉዳዮች በይኖ የሚዳስስ "እናት" የተሰኘ መፅሐፍ ተመርቆ ለውይይት ቀርቧል። መፅሐፉን በዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ዶ/ር ይሁኔ አየለ ናቸው የፃፉት።
በመድረኩ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንትን ወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ዳዊት ሀዬሶ (ዶ/ር) የአስ/ተማ/አገ/ምክትል ፕሬዝዳንት፤ የሴቶች ትግል ከጥንት ጀምሮ እየተቀጣጠለ እየጨመረ የመጣ ነው ብለዋል።

በጣሊያን ቱሪን ዩኒቨርሲቲ የሚገኙት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ

ዲ.ዩ፦ መጋቢት 06/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በተማሪዎች የልውውጥ ፕሮግራም በጣሊያን ሀገር ቱሪን ዩኒቨርሲቲ የሚገኙት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች በሀገሪቱ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።
በቱሪን ዩኒቨርሲቲ ለስድስት ወራት ልምድ ለመለዋወጥ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ የሄዱት ስድስቱ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች በቱሪን ከተማ በሚገኘው በጣሊያን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ቆንስላ ፅ/ቤት ነው ውይይቱን ያደረጉት።
በውይይቱ የኤምባሲው ምክትል ሚሲዮን አቶ አሰፋ አብዩ እና አቶ ደሳለኝ መኮንን የተገኙ ሲሆን ከአምባሳደር ደሚቱ አምቢሳ ለተማሪዎቹ የተላከ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክትን አድርሰዋል።

በአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ

በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ሀገር አቀፍ ወስዳችሁ፣ በአቅም ማሻሻያ (remedial) ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ወደ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የምትገቡበት ቀን ከመጋቢት 14-15/2015 ዓ.ም መሆኑን እንገልፃለን።

Pages