Day-3 Heart Convention, 2021, MoSHE

ሦስተኛ ቀኑን የያዘው "ወደ ዕውቀት-መር ኢኮኖሚ" በሚል መሪ ቃል በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተዘጋጀው HEART Convention 2021 በዛሬው ውሎ በዋናነት በድጅታል ስትራቴጂ እና በኢንዱስትሪ ሊንኬጅ ጉዳዮች ላይ እየመከረ ይገኛል::
የምርምር÷ የፈጠራና የጉድኝት ስራዎችን ለማበረታታት ታስቦ በተዘጋጀው በዚህ ኮንቬንሽን ላይ ዩኒቨርሲቲዎች÷ የቴክኒክና ሙያ እና የተለያዩ የምርምርና የፈጠራ ተቋማት እየተሳተፉ የሚገኙ ሲሆን ዲላ ዩኒቨርሲቲም በምርምር÷ በፈጠራ እና በኢንዱስትሪ ግንኙነት ስራዎች የተከናወኑትን ተግባራት ለታዳምያን እያቀረበ ይገኛል::
 
ሐምሌ 7 ቀን 2013 ዓ.ም.
ኢንተርኮንትነንታል ሆቴል, አዲስ አበባ, ኢትዮጵያ