ዲ.ዩ፤ ሚያዝያ 7/2016 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና እንደሚጫወቱ የተገለጸው የትምህርት ጥራትና ማሻሻያ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት “Empowering Academic Advisors Trough Training for Sustainable Quality” በሚል መሪ ሀሳብ ለአማካሪ መምህራን በተሰጠው ስልጠና ላይ ነው ።
ታምራት በየነ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት በመርሃ ግብሩ ባደረጉት ንግግር፤ እየታየ ያለውን የትምህርት ጥራት መጓደል ለማስተካከል እንደ አገር እንዲሁም እንደተቋም ሪፎርም ለማድረግ የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ እንደሚገኙ ጠቁመው፤ መምህራን በትምህርት፣ በምርምር፣ በስልጠና እንዲሁም ልምድና ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ አቅምን ለማሳደግና የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል።
ዶ/ር ታምራት አክለውም፤ የዛሬው ስልጠና አማካሪ መምህራን (Academic Advisors) ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት፣ ሙያዊ ልምድ ልውውጥና መነቃቃትን በመጨመር ተማሪዎቻቸውን በቅንነትና በታታሪነት በማገልገል በተቋሙ በሚሰጠው ምዘና ተማሪዎች አጥጋቢ ውጤት እንዲያመጡ፣ በአገር አቀፍ ጀረጃ የሚሰጠውን የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና በብቃት አልፈው በገበያው ላይ ተወዳዳሪና በሙያቸው ተፈላጊ የሆኑ ምሩቃንን ለማፍራት መምህራን የማይተካ ሚና እንደሚጫወቱ አስገንዝበዋል ።
በቀለ መንገሻ (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትና ማሻሻያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በበኩላቸው፤ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ መምህራን የማይተካ ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በማሰብ በሁሉም ኮሌጆች እና ትምህርት ቤቶች የሚገኙ አማካሪ መምህራን በዘርፉ በቂ እውቀትና ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች ለአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠቱን ገልጸዋል።
ቸርነት አይተንፍሱ (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የትምህርትና ሥነ-ባሕርይ ተቋም መምህርና ተማራማሪ እንዲሁም የእለቱ አሰልጣኝ ስልጠናው የአማካሪ ምንነትና ክህሎት፣ ባሕርይ፣ የተመካሪ ምንነትና ባሕርይ፣ የአማካሪና ተመካሪ ግንኙነት፣ የዩኒቨርስቲው የሴኔት ‘ሌጂስሌሽን’ ስለ አካዳሚክ ማማከር ያስቀመጣቸውን መምሪያና ደንቦች እና ተያያዥ ጉዳዮች፣ ከተሞክሮዎች ጋር በማያያዝ የግንዛቤ ማስጨበጫ መሰጠቱን ገልጸዋል።
በስልጠናው ከታሳፉ መምህራን መካከል መምህር ድረስ ማሞ በሰጡን አስተያየት፤ ከተማሪዎች ጋር ያለውን ግንኙነት ጤናማ በማድረግ እንደ ተቋምና እንደ ሀገር እንዴት ውጤታማ መሆን እንደሚቻል ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት እንዲሁም የህይወት ልምድና ተሞክሮዎችን ያገኙበት ስልጠና መሆኑን ነግረውናል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
Facebook:
https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et









