Dilla University

News
Training Provided on Research Ethics and Integrity

Training Provided on Research Ethics and Integrity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

Call For Papers

Call For Papers

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ የካቲት 17/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በቡና አዘገጃጀትና ጥራት ምርመራ ላይ በጌዴኦ ዞን ለሚገኙ ሕብረት ስራ ማሕበራት የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።
አለሙ ደሳ (ዶ/ር)፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የቡና ምርምርና ስልጠና ተቋም ዳይሬክተር በመርሀ ግብሩ ላይ ባሰሙት ንግግር፤ ዩኒቨርሲቲው በሀገርና በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ቡና የሚመረትበት አከባቢ የሚገኝ በመሆኑ ለቡና ልማት ትኩረት በመስጠት የተለያዩ ስራዎች በመከወን ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰው ቡና የሀገራችን የውጭ ምንዛሬ በማስገኘት ለብዙ ሚሊዮን ህዝብ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የገቢ ምንጭ መሆኑን አንስተዋል።
ዶክተር አለሙ አያይዘውም፣ በአዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ በተደረገው የተልዕኮ ልየታ መሰረት በቡና ልማትና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ የልህቀት ማዕከል ለመሆን ምርምሮችን በመስራት፣ በምርምር የለማ ቡና ለማሕበረሰብ በመስጠትና በአገርና በአለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ፣ ስርዓተ ትምህርት በመቅረጽ በቡና መስክ ሁለተኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም በመክፈት፣ የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች መስጠት፣ የቡና ምርምር የልህቀት ማዕከል ማደራጀትና ሌሎች ስራዎችን በመስራት የቡና ምርታማነት ጥራትን በመሻሻል ለአካባቢው ማሕበረሰብና ለአገር ጥቅም እንዲያስገኝ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስረድቷል።
መምህር ብሩህ ተስፋሁን፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት የአጫጭር ስልጠናዎች አስተባባሪ በበኩላቸው፤ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለማሕበረሰቡ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች የቡና ልማት አንዱ መሆኑን ገልጸው፤ በቡና ልማት ዙሪያ በተለያዩ ጊዜያት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሲሰጥ መቆየቱንና ይህን ስልጠናም በጌዴኦ ዞን ለሚገኙ 28 የቡና ሕብረት ስራ ማሕበራት ኢንዱስትሪ ባለሙያዎች በዘርፉ በቂ እውቀትና ልምድ ባላቸው የዩኒቨርስቲው መምህራን በቡና አዘገጃጀትና ጥራት ምርመራ ሲሰጥ መቆየቱን እንዲሁም ስልጠናውን ወደ ተግባር ለመቀየር የሚረዳቸውን ዕቅድ አዘጋጅተው በቀጣይ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በቅንጅት የሚሰሩበትን የጋራ ስርዓት መዘርጋቱን ተናግረዋል።
ስልጠናውን ከሰጡ መምህራን መካከል መምህር እስማኤል ከሊል፣ በግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ኮሌጅ የሆርቲካልቸር መምህርና በቡና ዘርፍ ተማራማሪ፤ ስልጠናው በአለም አቀፍ ደረጃ በጣዕሙ የሚታወቀውን የይርጋጨፌ የቡና እውቅናውን ጠብቆ እንዲዘልቅና ጥራት ያለውን የቡና ምርት ወደ ገበያ በማቅረብ አርሶ አደሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የሚገባቸውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንዲያገኙ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል።
ሥልጠናው ከቡና ችግኝ አዘገጃጀት ጀምሮ እስከ አፍልቶ መጠጣት ያለውን ሂደት የሸፈነ፤ የአካባቢውን ጥበቃ፣ የውሃ ብክለትና መፍትሔ፣ የገበያ ትስስርና የዓለም ቡና ገበያ ሁኔታና ሌሎች ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ያካተተ ጥሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሰጠቱን መምህር እስማኤል ከሊል ገልጸዋል።
ከሰልጣኞች መካከል አቶ ብርሀኑ ዋቆ እና አቶ ተስፋዬ ሚሊዲጋ በሰጡን አስተያየት፤ ስልጠናው ተግባር ተኮር፣ ከሙያቸውና ስራቸው ጋር የሚሄድ ተጨማሪ እውቀትና ክህሎት ያገኙት መሆኑን ገልጸው፤ ያገኙትን እውቀትና ክህሎት ለስራ ባልደረቦቻቸውና ለአርሶአደሮች በማካፈል ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለገበያ በማቅረብ አርሶአደሮች የልፋታቸውን ዋጋ እንዲያገኙ እንዲሁም አገራችን ከፍ ያለ የውጭ ምንዛሬ እንድታገኝ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ነግረውናል።
ዲላ፤
የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲዲላ፤
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት
Facebook: https://www.facebook.com/Du.edu.et
Telegram: https://www.t.me
website: https://www.du.edu.et
Email: https://www.pirdir@du.edu.et