Dilla University

News
Training Provided on Research Ethics and Integrity

Training Provided on Research Ethics and Integrity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ምረቃ ስነ-ስርዓት

Call For Papers

Call For Papers

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University became the first Ethiopian Public university Certified on a Good Financial Grant Practice (GFGP)

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Dilla University Held Its Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Upcoming Event: Dilla University’s Annual Research Validation Workshop

Call for paper

Call for paper

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

6th Science Week Symposium: Robotics and Artificial Intelligence for Societal Transformation

Call For Research Propossals

Call For Research Propossals

Upcoming Event

Upcoming Event

Green University, Sustainable Future

Top News

ዲ.ዩ፤ ህዳር 30/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች፣ ህፃናት እና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት ከኢንተርፕሩነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በአለም አቀፍ ደረጃ ለ32ኛ ጊዜ በሀገራችን ኢትዮጵያ ለ18ኛ ጊዜ እየተከበረ ያለውን “መቼም የትም በምንም ሁኔታ ፆታዊ ጥቃትን ዝም አንበል” በሚል መሪ ሃሳብ ለተከታታይ 6 ቀናት የሚከበረው የነጭ ሪቫን ቀንን በማስመልከት ለተቋሙ ሴት መምህራን ሲሰጥ የቆየው የሥራ ፈጠራ የአሰልጣኞች ስልጠና ተጠናቋል።

ወ/ሮ አለሚቱ ብርሃኑ፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች፣ ህፃናት እና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክተር፤ 40 ለሚሆኑ የተቋሙ ሴት መምህራን የስራ ፈጠራ የአሰልጣኞች ስልጠና መሰጠቱን ገልጸው፤ ሰልጣኝ መምህራን ተማሪዎቻቸውን ሥራ ፈጣሪ ለማድረግ እንዲሁም ራሳቸውንም የቢዝነስ አስተሳሰብ ይዘው የተሻለ ነገር እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የስራ ፈጠራ ክህሎት እንዴት እንደሚያዳብር ግንዛቤ የተገኘበት፤ እራሳቸውን ያዩበት፣ ተማሪዎቻቸው ላይ ተጽዕኖ መፍጠር በሚችሉበት ሁኔታ ላይ የተሰጠ ስልጠና መሆኑን አያይዘው ገልጸዋል።

ወ/ሮ ጽጌረዳ ወ/ሚካኤል፣ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ኢንስቲትዩት አሰልጣኝና የቢዝነስ አማካሪ በበኩላቸው፤ የሥራ ፈጠራ ስልጠና በአለም አቀፍ ደረጃ የሚሰጥ ስልጠና መሆኑንና ገልጸው በተመሳሳይ በኢትዮጵያ በሁሉም ክልሎች እየተሰጠ ያለ ስልጠና መሆኑን አስገንዝበዋል። በስልጠናው ላይ መምህራኑ በሙሉ አቅም ተሳትፎ እንደነበራቸውም አውስተዋል።

ወ/ሮ ወንጌል የሸዋልዑል እና አቶ ተመስገን አብርሃ የኢንተርፕርነርሽፕ ልማት ማዕከል አሰልጣኝ በበኩላቸው፤ የስልጠናው አላማ ሰዎች የባህሪ ለውጥ እንዲያመጡ የባህሪ ለውጥ ላይ ያተኮረ መሆኑን አስረድተው ሰዎችን የሥራ ፈጣሪነት አቅማቸውን የሚለኩበት እንደሆነም አስገንዝበዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ፣ ዶ/ር አለማየሁ አካሉ በበኩላቸው፤ ዲላ ዩኒቨርሲቲ አሁን በሀገሪቱ ከሚገኙ 15 የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ መሆኑንና የአፕላይድ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲዎች በተልዕኮ ልየታቸው ከተሰጣቸው አምስት መሠረታዊ ነገሮች አንዱ የስራ ፈጣሪነት እሳቤን ማጎልበት መሆኑን አስረድተዋል።

ዶ/ር አለማየሁ አክለውም፤ ከኢንዱስትሪዎች ጋር የሚኖርን ትስስር በማጠናከር ኢንዱስትሪዎችን የሚፈጥርና ችግሮቻቸውን የሚፈታ፣ አዳዲስ የቢዝነስ አስተሳሰብ ያላቸውን ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን አስተማሪዎችንም ጭምር መፍጠር እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል።

ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል የስፖርት ሳይንስ መምህርት እና የትምህርት ጥራት ም/ዳይሬክተር ናርዶስ ኤልያስ እና የሀይድሮሊክስና ውሃ ምህንድስና ት/ክፍል መምህርት እንዲሁም የፍሬሽ ማን ፕሮግራም አስተባባሪ ቤተልሄም በለጠ፤ ወደ ቢዝነስ ለመግባት ምን አይነት ባህሪ ሊኖረን ይገባል የሚለውን የተገነዘብንበት፣ የራስን ገቢ ማመንጨት የምንችልባቸው ነገሮች ምንድን ናቸው የሚለውን የፈተሽንበት ነው ሲሉ ይገልጻሉ። ስልጠናውን በትክክል ለተሳተፉ ሰልጣኞች የእውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡