የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞቾ ልማት ድርጅት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ትምህርት ድጋፍ ማዕከል ጋር በመተባበር ተማሪዎች ስልጠና ሰጠ።

ዲ.ዩ የካቲት 21/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞቾ ልማት ድርጅት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ትምህርት ድጋፍ ማዕከል ጋር በመተባበር ለተማሪዎች ስልጠና ሰጠ። ስልጠናው በአካል ጉዳተኝነት አና አካታችነት ጽንሰሀሳብ ዙሪያ ከየኮሌጁ ለተውጣጡ ጉዳት አልባ ተማሪዎች ተሠጥቷል፡፡
ተማሪዎች በጋራ በሚኖሩባቸው ቦታቸው፣ በመማሪያ ክፍላቸውና በእለት ተዕለት የጊቢ እንቅስቃሴያቸውም ሆነ ወደ ስራ አለም ሲቀላቀሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ለሚያገኟቸው አካል ጉዳተኞች የሚኖራቸው መስተጋብር የተሻለ እንዲሆን ለማድረግ ታልሞ መዘጋጀቱን የልዩ ፍላጎት ት/ት ድጋፍ ማዕከል ዳይሬክተር ዶ/ር አባቡ ተሾመ ገልጸዋል።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ በገቢ ግብር አዋጅ እና መመሪያዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ስልጠና ተሰጠ።

ዲ.ዩ የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የኢፌዲሪ ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ የግዢ ፣ የፋይናንስና የውስጥ ኦዲት ባለሙያዎች በግዢ ግብር አዋጅ እና መመሪያዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ስልጠና ተሰጠ።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ በግንባታ ላይ ያሉትን የአስተዳደር ህንፃ እና ሀሴዴላ ግቢ ጎበኘ::

ዲ.ዩ የካቲት 19/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ እና የዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራር የ2014 ዓ.ም የስድስት ወር እቅድ ክንውን ላይ ውይይት ካካሄደ በኋላ በኦዳያአ ግቢ የሚገኘውን የአስተዳደር ህንፃ እና የሀሴዴላ ግቢ አጠቃላይ የግንባታ ሂደት ጎብኝቷል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ ከሚባሉ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ በመሆኑ ተቋሙን የሚመጥን የአስተዳደር ህንፃ መገንባቱ የሚያስደስት ነው ያሉት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ አብዮት ደምሴ፣ ግዙፉ የአስተዳደር ህንፃ ከዚህ በፊት የነበረውን የቢሮ እጥረት በመቅረፍ እና ምቹ የስራ ቦታ በመፍጠር እረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል።
ቦርዱም ዩንቨርሲቲው የሚሰራቸው ስራዎች ላይ የቅርብ ክትትል እና ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ እፅዋት ጥበቃ እና ኢኮቱርዝም ማዕከል "የኢኮቱርዝም ልማት ለአከባቢ ብዝሃ ሕይወት ጥበቃ እና ለስራ ዕድል ፈጠራ" በሚል መሪ ቃል ውይይት አካሄደ::

ዲ.ዩ. የካቲት 19/2014 ዓ ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ እፅዋት ጥበቃ እና ኢኮቱርዝም ማዕከል "የኢኮቱርዝም ልማት ለአከባቢ ብዝሃ-ሕይወት ጥበቃ እና ለስራ ዕድል ፈጠራ" በሚል መሪ ቃል ውይይት አካሄደ። በውይይቱም የዲላ ከተማ፣ አባያ እና ዳራ ወረዳ አመራር አካላት ተሳትፈዋል።
የአካባቢ ብዝሃ-ሕይወት ለመጠበቅ የተፈጥሮን ጸጋ በምርምር በመለየት ወደ ሀብትነት መቀየር ይገባል። ስለሆነም አመራሮች እና የአከባቢው ማህበረሰብ ስለ ብዝሃ-ሕይወት ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማዲረግ፣ የኢኮቱርዝም አገልግሎትን ለማጠናከር ታስቦ ነው ይህ ውይይት የተዘጋጀው ብለዋል አቶ ምትኩ ማኑዳ የዲላ ዩኒቨርሲቲ እፅዋት ጥበቃ እና ኢኮቱርዝም ማዕከል ዳሬክተር።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተዘጋጀውን የማሕበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብዕ ዘርፍ የቀድመ-ምረቃ ሥርዓት ትምህርት በመቅረፅ እና በማስተባበር ለተሳትፉ ባለ ድርሻ አካላት የምስጋና ዕውቅና ፕሮግራም አከናወነ::

ዲ.ዩ የካቲት 17/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በ2013 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሄደው የማሕበራዊ ሳይንስና ሥነ-ሰብዕ ዘርፍ የቅድመ-ምረቃ ስርዓት ትምህርት በመቅረፅ እና በማስተባበር ለተሳተፉ ባለ ድርሻ አካላት በዛሬው እለት የምስጋና እና እውቅና ምስክር ወረቀት መስጠቱን ዲላ ዩኒቨርስቲ አስታወቀ። የእውቅና መርሃ-ግብሩን የዩኒቨርስቲው ማህበራዊ ሳይንስና ስነ-ሰብዕ ኮሌጅ አስተባብሮ አዘጋጅቶታል፡፡
ማሕበራዊ ሳይንስ እና ስነ-ሰብዕ ኮሌጅ በዩኒቨርሲቲያው ካሉ ኮሌጆች አንጋፋ እና በውስጡ የያዛቸው ትምህርት ክፍሎችም ሰፊ ናቸው ያሉት ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አገራችንና ተቋማችን የሰጣችሁን ሀላፊነት በብቃት ስለተወጣችሁ በኢ.ፌ.ድ.ሪ ትምህርት ሚኒስተር እና በዩኒቨርሲቲው ስም አመሰግናለው ብለዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት አባላት ተማሪዎችን ለመቀበል ቅድመ ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ያለውን የሀሴ ዴላ ካምፓስ ጉብኝት አካሄዱ።

ዲ.ዩ የካቲት 17 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት አባላት አራተኛ ካምፓስ በሆነው ሀሴ ዴላ ካምፓስ ተገኝተው የመስክ ጉብኝት አካሄዱ።
በዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ በተመራው በዚህ ጉብኝት ወቅት ካምፓሱ ተማሪ ለመቀበል ያለውን ቅድመ ዝግጅት ምን እንደሚመስል በየዘርፉ ያሉ ኃላፊዎች ማብራሪያ ለማኔጅመንቱ የሰጡ ሲሆን የሀሴ ዴላ ካምፓስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ታምራት ፍርዴ በበኩላቸው በአሁኑ ሰዓት ግብዓቶችን ለማቅረብ ጨረታ ያሸነፉ ድርጅቶች አንዳንድ ግብዓት ማዘግየት ካልሆነ በስተቀር የፊንሽንግ ስራው በጥሩ ሁኔታ እየሄደ መሆኑን ተናግረው እነዚህ ድርጅቶችንም ቢሆን በአካል እስከ ተቋሟቸው ድረስ በመሄድ በፍጥነት ግብዓቶችን እንዲያቀርቡ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ዲ.ዩ. የካቲት 15/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መፃህፍት እና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ፣ ከደቡብ ቤ/ብ/ሕ/ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እና ዲላ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ያዘጋጁት የንባብና መፃህፍት አውደ-ርዕይ ሳምንት አካል የሆነው በሰነድ፣ መዛግብት እና የፅሁፍ ቅርሶች አያያዝ እና አስተዳደር ዙሪያ የፓናል ውይይት ተካሄደ። በዲላ ከተማ የጌዴኦ ባህል አዳራሽ የተካሄደው

ዲ.ዩ. የካቲት 15/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መፃህፍት እና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ፣ ከደቡብ ቤ/ብ/ሕ/ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እና ዲላ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ያዘጋጁት የንባብና መፃህፍት አውደ-ርዕይ ሳምንት አካል የሆነው በሰነድ፣ መዛግብት እና የፅሁፍ ቅርሶች አያያዝ እና አስተዳደር ዙሪያ የፓናል ውይይት ተካሄደ።
በዲላ ከተማ የጌዴኦ ባህል አዳራሽ የተካሄደውን የፓናል ውይይት በንግግር የከፈቱት አቶ ዘማች ክፍሌ የጌዴኦ ዞን ትምህርት መመሪያ ኃላፊ እና የዞኑ አስተዳደር ተወካይ ናቸው። ኃላፊው በንግግራቸው እንዳሉት ሰው ለአካላዊ ጥንካሬው መዳበር ምግብ እንደሚሻ ሁሉ ሁሉን አቀፍ እይታና አስተሳሰቡ እንዲዳብር ደግሞ በትምህርት እና ንባብ የዳበረ እሳቤ ያስፈልጋል ብለዋል።

Pages