ምርምር ስራዎች ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

ዲ.ዩ፦ ሕዳር 19/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ ቤት ከምርምርና ስርጸት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር በምርምር ስራዎች ዙርያ ሁለተኛ ዙር የውይይት መድረክ አካሂዷል።
ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በአሜሪካ ኢምባሲ ጋባዥነት ዘጠኝ የዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንቶች፣ አስራ አምስት ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም ሁለት የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያዎች የተካተቱበት ጉብኝት በአሜሪካ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች አደርገው መመለሳቸው ይታወሳል።
ዶ/ር ችሮታው በአሜሪካ ቴክሳስ ቴክ፣ ኦክላሆማ ስቴት እና ኦሃዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲዎችን በጎበኙበት ወቅት ያገኙትን ልምድ ለጉባኤው ተሳታፊዎች አካፍለዋል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ‘‘ቴክኖ ሰርቭ’’ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ‘‘ቴክኖ ሰርቭ’’ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ
ዲ.ዩ፦ ህዳር 17/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ ‘‘ቴክኖ ሰርቭ’’ ከተባለ የግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በቡና ልማት ዙርያ አብሮ ለመስራት የስምምነት ሰነድ መፈራረሙ ተገልጿል።
ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት፤ አካባቢው እምቅ የቡና ሀብት ያለበት እንደመሆኑ መጠን ይህንን ለአከባቢው ማሕበረሰብ እና አገር እድገት ከፍተኛ ሚና እንዲኖረው በሳይንሳዊ ምርምር ለመደገፍ ሰፊ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የሳይንስ ሳምንት መርሃግብር ተጠናቀቀ

ዲ.ዩ፦ ህዳር 16/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ስርፀት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት "ሳይንስ ለምግብ ዋስትና እና ሉአላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ ሲከናወን የቆየው አራተኛው የሳይንስ ሳምንት ፍጻሜውን አግኝቷል።
በመርሃግብሩ ወቅት ንግግር ያደረጉት ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት በሀገራችን አመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞችንና ለም መሬት ይዘን የምግብ ዋስትናችንን ባለማረጋገጣችን ምክንያት በተጽእኖ ውስጥ እንድንወድቅ ሆነናል ብለዋል።
አያይዘውም ሀገሪቷ ያስተማረቻቸው ምሁራን በአገራችን ያለውን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የተሻለ ስራ ለመስራት ጥናትና ምርምር ማድረግ እንዲሁም ጥናቱን ወደ ተግባር መለወጥ ይጠበቅብናል ሲሉ አሳስበዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርደ በዩኒቨርሲቲው ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ ከተቋሙ ከፍተኛ አመራር ጋር ተወያየ

ዜና ትንታኔ ዲ.ዩ፡- ህዳር 03/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ በዩኒቨርሲቲው የ2014 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2015 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ዝርዝር ውይይት አካሄደ፡፡ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዋ እና የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እና የስራ አመራር ቦርዱ አባላት በውይይቱ ተገኝተዋል፡፡ በእለቱ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በአራቱ የምክትል ፕሬዝዳንት ፅ/ቤቶች፣ በህክማና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል እንዲሁም የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት እና በስሩ ያሉ ባለ ብዙ ዘርፍ ፅ/ቤቶች ባለፈው አመት ያከናወኗቸው ተግባራት አፈፃፀም ሪፖርቶች ቀርበዋል፡፡ በዝርዝር ሪፖርቶቹ በአመቱ የታቀዱ፣ የተከናወኑ ተግባራት እንዲሁም በአፈፃፀም የተገኙ እምርታዎች እና ጉድለቶች ከተወሰዱ መፍትሄዎች ጋር በዝርዝር ተዳስሰዋል፡፡ የበጀት ዓመቱን የመማር ማስተማር ተግባራት ዝርዝር ሪፖርት ያቀረቡት የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍቃዱ ወ/ማርያም በዓመቱ

የ‹ሲ.ቲ ስካን› ማሽን ስራ መጀመሩ ተገለጸ

ዲ.ዩ፡- ጥቅምት 15/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል ከ45 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገዛው የ‹ሲ.ቲ ስካን› ማሽን ስራ መጀመሩ ተገለጸ፡፡ ሆስፒታሉ የህክምና ስራዎቹን ለማሳለጥ እና ተደራሽነት ለማስፋት ከሚጠቀመው ዘመናዊ የሕክምና መሳሪያዎች አንዱ መሆኑን ነዉ የተገለጸው። በዩኒቨርሲቲው የሕክምና እና ሳይንስ ኮሌጅ እና ጠቅላላ ሆስፒታል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምጽዋ ሩፎ ሆስፒታሉ ከጌዴኦ ዞን፣ ኦሮሚያ እና ሲዳማ አጎራባች ክልሎች ለሚመጡ ከፍተኛ ቁጥር ላለው ሕብረተሰብ የሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል፡፡ ለሕብረተሰቡ ከሚሰጣቸው የህክምና አገልግቶች በተጨማሪ ሆስፒታሉ በጤና ዘርፍ ተማሪዎችን በተለያዩ የሕክምና ሙያ መስኮች ተቀብሎ እያስተማረ እና እያሰለጠነ እንደሚገኝም ዶ/ር ምፅዋ ገልፀዋል፡፡ እሳቸው አክለውም አዲስ የተገዛው ‹ሲ.ቲ ስካን› በዚህ ሳምንት ስራ ጀምሯል ብለዋል፡፡ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ጠቅላላ ሆስፒታ

For all Regular Students of Dilla University

1) If you are a first-year (freshman) student and will start your second semester, you will report on Tikimt (ጥቅምት) 28 and 29, 2015 e.c.
2) Third year and above (3rd, 4th, and 5th) year students, we would like to inform you that the dates you will have to come and register at the university are Hidar (ህዳር) 05 and 06, 2015 e.c.
3) Students from the Health and Medical Sciences College will report according to the previous call.

Pages